የአንጎላ የተኩስ አቁም ጥሪ
እሑድ፣ መጋቢት 7 2017ማስታወቂያ
ፕሬዚዳንቱ ትናንት ቅዳሜ ምሽት ባወጡት መግለጫ «በተኩስ አቁሙ በሲቪሊያዉያን ላይ ሊደርሱ የሚችሉ ጥቃቶችን ጨምሮ አዳዲስ ቦታዎችን ለመቆጣጠር የሚደረጉ ጥረቶችን ማስቆምን»ማካተት ይኖርበታል ብለዋል።
የኮንጎው ፕሬዝዳንት ፌሊክስ ቲሺሴኬዲ ከአማጺው የኤም 23 ታጣቂ ቡድን ጋር ለመደራደር ከአንድ ዓመት በላይ ፈቃደኝነታቸው ሳያሳዩ መቆየታቸው ይነገራል።
ነገር ግን ፕሬዚዳንቱ በቅርቡ ወደ ሉዋንዳ ካደረጉት ጉዞ በኋላ ከአማጽያኑ ጋር ፊት ለፊት ለመነጋገር መዘጋጀታቸውን ካሳወቁ በኋላ አንጎላ የፊታችን ማክሰኞ የሚደረገው እና በርካቶች የሚጠብቁትን ድርድር ታስተናግዳለች።
የኤም 23 አማጽያን ካለፈው ጥር ወር አንስተው በከፈቱት መጠነ ሰፊ የማጥቃት እርምጃ የምስራቃዊ ኮንጎዋ የጎማ ከተማን ጨምሮ በርካታ አካባቢዎችን በቁጥጥራቸው ስር አዉለዋል።