ማስታወቂያ
ኢትዮጵያ በአንድ ወቅት ወባ ማጥፊያ የሚባል ድርጅት ነበራት። ወባን ማጥፋት ባለመቻሉ ወባን ስለመከላከል ዛሬም መነጋገር ግድ ሆኗል። ለዚህ ደግሞ ሞቃትና ርጥበት አዘል የአየር ጠባይ የሚመቻት የወባ ትንኝ ባህርይ ብቻ ሳይሆን ማባሪያ ያጣው ግጭት ጦርነትም ቁጥጥር ክትትሉን ማደናቀፉ አይነተኛ ምክንያት ሆኗል።
ከተወሰኑ ዓመታት በፊት ኢትዮጵያ ውስጥ በበርካታ አካባቢዎች የወባ ስርጭትን መቆጣጠር የመቻሉ የስኬት ዜና ይነገር ነበር። በተለይም በድሬደዋና አካባቢው ከ12 ዓመታት በፊት የወባ በሽታ ታሪክ ሊሆን መቃረቡን የከተማዋ የጤና ጉዳይ ባለሥልጣናትን በማነጋገር ለውጤት ያበቃቸውን ጥረት የተመለከቱ መረጃዎችን ማቅረባችን ይታወስ ይሆናል።
ወባ ላይ ለዓመታት የሠሩት የኅብረተሰብ ጤና ባለሙያው ዶክተር መኮንን አይችሉህም የወባ ስርጭትን ለመግታት ያላሰለሰ የክትትል ሥራ መሥራት እንደሚያስፈልግ ይናገራሉ።