ከእንግዲህ የልብ ህሙማንን በአገር ዉስጥ ማከም ይቻላል
ማክሰኞ፣ የካቲት 10 2001ማስታወቂያ
ይህ ብስራት የተማዉ ባለፈዉ ሳምንት ነዉ። ሃኪም ቤቱ በበጎ አድራጊዎች ርብርብ ተገንብቶ ስራ መጀመሩ በስራዉ ለተሳተፉ ታታሪዎች ብቻ ሳይሆን ዜናዉን ለሚሰሙት ሁሉ አመርቂነቱ አያነጋግርም። የሃኪም ቤቱ አገልግሎት እንዳጀማመሩ ለህፃናት ብቻ ሳይሆን አዋቂዎችንም ያካትታል። በቀጣይም የምርምር ማዕከል የሚገነባ ሲሆን ባለሙያዎችን ማሰልጠንኑም በተጓዳኝ ይከወናል።