ከባድ አውሎነፋስ በጀርመን ጥፋት አደረሰ
ሰኞ፣ የካቲት 2 2012ማስታወቂያ
«ዛቢነ» የሚል መጠሪያ የተሰጠው እና ከትናንት እሁድ ጀምሮ የጀርመን የተለያዩ ክፍለ ሃገራትን እያመሰ የሚገኘው አውሎ ነፋስ በሰው እና በንብረት ላይ ጉዳት ማድረሱን ፖሊስ እና የእሳት አደጋ መከላከያ የገለፁ ነው። የረዥም ርቀት ተጓዥ ባቡር እና የአውሮፕላን በረራዎች ከትናንት ጀምረው ተስተጓጉለዋል። በሰዓት እስከ 170 ኪሎ ሜትር እንደሚገሰግስ የተነገረለት አውሎነፋሱ ከጀርመን ባሻገር የአጎራባች የአውሮጳ ሃገራትንም ማዳረሱን ቀጥሏል። በጀርመን በአንዳንድ አካባቢዎች የመሠረተ ልማት ላይ ጉዳት አድርሷል ፤ የዕለት ተዕለት እንቅስቃሴንም አስተጓጉሏል።
ይልማ ኃይለ ሚካኤል
ታምራት ዲንሳ
ሸዋዬ ለገሠ