ወይዘሮ ነጻነት በዶቼቬለ ሲታወሱ
ማክሰኞ፣ መጋቢት 1 2012ማስታወቂያ
የቀድሞ ጋዜጠኛ እና የኢትዮጵያ መንግሥት ከፍተኛ ባለሥልጣን ወይዘሮ ነጻነት አስፋው የህዝባዊ ወያኔ ሐርነት ትግራይን የትጥቅ ትግል ከመቀላቀላቸው በፊት በዶቼቬለ በራድዮ ጋዜጠኝነት ሰርተዋል። ከዚያ አስቀድሞም በኢትዮጵያ ማስታወቂያ ሚኒስቴር በተመሳሳይ ሥራ ውስጥ ነበሩ። ቦጋለ መኩሪያ በጎርጎሮሳዊው 1970 ዎቹ ከወይዘሮ ነጻነት ጋር ዶቼቬለ ይሰሩ ከነበሩት ጋዜጠኞች መካከል አንዱ ነው። በአሁኑ ጊዜ ጀርመን ውስጥ በጡረታ ላይ የሚገኘው ጋዜጠኛ ቦጋለ ከጀርመን ድምጽ ራድዮ ዶቼቬለ መሥራቾች አንዱ ነው። ኂሩት መለሰ አነጋግራዋለች።
ኂሩት መለሰ
ማንተጋፍቶት ስለሺ