ፖለቲካሰሜን አሜሪካ
እስራኤል ኢራንን መደብደቧ የፈጠረዉ ድንጋጤና የዩናይትድ ስቴትስ ተቃራኒ አቋም
ዓርብ፣ ሰኔ 6 2017ማስታወቂያ
እስራኤል፣ ኢራንን መደብደቧ የዓለምን የወትሮ እንቅስቃሴ አሽመድምዶታል። የኢራን፣የእስራኤል፣ የሶሪያና የሌሎች ያካባቢዉ ሐገር የአየር ክልልሎች ተዘግተዋል። አብዛኞቹ ዓየር መንገደች ከና ወደ መካከለኛዉ ምሥራቅ የሚያደርጉትን በረራ ሠርዘዋል።
የነዳጅ ዘይት ዋጋ በ9% አሻቅቧል። ኢራን ላፀፋ ጥቃት እየዛተች ነዉ። የፀጥታዉ ጥበቃ ምክር ቤት በጉዳዩ ላይ ለመነጋገር ዛሬ ይሰበሰባል።
አብዛኞቹ የመካከለኛዉ ምሥራቅ፣የእስያ፣ የቱርክና የሩሲያ መንግሥታት የእስራኤልን ርምጃ ሲያወግዙ የምዕራብ አዉሮጳ መንግሥታት ግጭቱ እንዳይባባስ እየተማፀኑ ነዉ።
ለእስራኤል ሁለንተናዊ ድጋፍ የሚሰጡት የዩናይትድ ስቴትስ ባለሥልጣናት ግን ባንድ በኩል በጥቃቱ «የለንበትም» ሲሉ፣ በሌላ በኩል ግን ኢራን የከፋ ድብደባ እንደሚደርስባት እየፎከሩ ነዉ።
አበበ ፈለቀን
ነጋሽ መሐመድ
ኂሩት መለሰ