በአውሮጳ ኮቪድ19 ያስከተለውን ቀውስ ለመታደግ የታቀደው መርሃ ግብርና ተቃውሞው
ሐሙስ፣ ግንቦት 20 2012ማስታወቂያ
የአውሮጳ ህብረት ኮሚሽን በኮቪድ 19 ምክንያት በህብረቱ አባል ሃገራት የደረሰውን የጤና ማህበራዊና ኤኮኖሚያዊ ቀውስ ለመታደግ ይረዳል ያለውን የኤኮኖሚ መርሃ ግብር ትናንት ብራሰልስ ለተሰየመው የአውሮጳ ፓርላማ አቅርቦ ይሁንታ አግኝቷል። ለመርሃ ግብሩ ተግባራዊነት የሁሉም አባል ሃገራት ስምምነት ያስፈልጋል።ይሁንና የጀርመን የፈረንሳይ የኢጣልያንን እና የስፓኝን ድጋፍ ያገኘው ይህ እቅድ ከስዊድን ከዴንማርክ ከኦስትሪያ እና ከኔዘርላንድስ ተቃውሞ ገጥሞታል።በእቅድ ላይ አባል ሃገራት የተለያየ አቋም መያዛቸው መርሃ ግብሩ እንደተፈለገው በአጭር ጊዜ ውስጥ መጽደቁን አጠራጣሪ አድርጎታል።
ገበያው ንጉሴ
ኂሩት መለሰ
ነጋሽ መሐመድ